Re: "ኢትዮጵያ አትፈርስም" እያሉ ኢትዮጵያን እያፈረሱ ይገኛሉ
"ኢትዮጵያ ለሶስት ትከፈላለች"? በምን መለኪያ?
የመጀመሪያው ስህተት የቀ.ሐ.ሥ ፌደሬሽኑን ማፍረስ ነው፣ አለ ልደቱ፤ እሺ!
አሁን ሌላ ስህተት ኤርትራን ማስገባት ነው፣ ይለናል፤
ስለዚህ ኢትዮጵያ አለቀላት አለ። ይሄ ሰውዬ እንዴት ነው የሚያስበው?
የኤርትራና ኢትዮጵያ በአሁኑ ጊዜ መቀራረብን ለምን ልደቱ ዕርግማን አድርጎ ይቆጥረዋል?
ጤነኛ ሰው መቀራረቡን እንደ እድል ይቆጥረዋል።
መረሳት የሌለበት ወያኔዎች ከኢሳይያስ በላይ የኤርትራ ጠበቃ ነን ይሉ ነበር።
ኤርትራንም በማስገንጠል ከኢሳይያስ በላይ እኛ ነን የሰራነው ብለው ፎክረዋል፤ ልደቱ ይህን በደንብ ያውቃል። ምን ተለወጠ?
ታዲያ አሁን የትሕነግ አለመኖርስ ማንን ይጎዳል?
ልደቱ ክህደቱን? ግብፅን?
ቀባጣሪ!