TAYE DENDA "አማራ ነን ብላችሁ ፈርሙ ወይም አከባቢዉን ልቀቁ" እየተባለ አማራነትን ለማጥመቅ የተያዘዉ ዘመቻ ከጁንታዉ ህወሀት በላይ ጁንታነት ይሆናል!
Posted: 10 Dec 2020, 16:08
አማራዉን የሚያጠቃዉ ማነዉ?
እዉነቱን እንነጋገር!
ትላንት አንድ ተረት ሰምቼ እጅግ ገርሞኛል! ተረቱ " ታዬ ደንደአ እንደ ስባት ነጋ አማራን በነገር ለማጥቃት የተመደበ ባለጊዜ ነዉ" ይላል። ለካ በኢትዮጵያ የሀሰት ትርክት ሲደረት የነበረዉ በዚህ መልክ ኖሯል? ግን ከአሁን በኋላ ማን በድሮ በሬ ያርሳል? ብልፅግና እዉነቱን በማጋለጥ ለፍትህ ይሰራል!
የአንድ ማህበረሰብ ጠላት ከማህበረሰቡ የሚነሳዉ ፅንፈኛ ነዉ። በ2ኛ የዓለም ጦርነት ጀርመንን ያወደማት ራሺያ ወይም አሜሪካ ሳይሆን ፅንፈኛዉ ናዚ መሆኑ ምስክር የማያሻዉ ሀቅ ነዉ! ይህ ለሌሎች ማህበረሰቦችም ይሰራል! ለመሆኑ አማራን እያጠቃ ያለዉ ማነዉ? በኔ እይታ የአማራ ህዝብ ዋነኛ ጠላት በአማራ ስም የሚፎክረዉ ፅንፈኛ ነዉ! የአማራ ፅንፈኞች "አማራነት የሰዉነት ዉሃ ልክ ነዉ! የደቡብ ሰዉ የሚማረዉ አማራ ለመሆን ነዉ! አማራ ከየመን ስለመጣ ከሌላዉ ብሔር በላይ ነዉ! " ሲሉ አማራ በወንድሞቹ ዘንድ በጥርጣሬ እንዲታይ በማድረግ ዘመድ መስለዉ እያጠቁት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል! የፅንፈኞቹን ናዚያዊ ፉከራ ሰምቶ ደስ የሚለዉ ወይም በግላጭ ለመቃወም የሚፈራዉ የአማራ ምሁር ወይም አመራርም አማራዉን ከማጥቃት አኳያ የድርሻዉን ይወስዳል! የኦሮሞ ፅንፈኞች " ሌላ ብሔር ያገባ ይፍታ! ዲቃላን እናጠፋለን! የጀግኖችን ደም እንበቀላለን! ነፍጠኛን ከኦሮሚያ እናባርራለን" ሲሉ ፊት ለፊት ገጥመን እና የህይወት ዋጋ ከፍለን በመታገል "የነፍጠኛ ተላላኪ" የተባልነዉ የስድብ ናፍቆት ኖሮብን ወይም የጓዶቻችን ህይወት ሳያሳዝነን ቀርቶ ሳይሆን በፅንፈኞች የወረደ ጀብደኝነት ኦሮሞ በወንድሞቹ ዘንድ ያለዉ ክብር እና ከፍታ እንዳይነካ ስንል መሆኑ ሁሉም ቢያዉቅ ይጠቅማል! የኦሮሞን ፅንፈኛ ስንታገል "ጀግና" እያለ ሲያወድሰን የነበረዉ ደግሞ ዛሬ የአማራ ፅንፈኛ ሲነካ "አካኪ ዘራፍ" ሲል ፍትህን የምንለካበት ሚዛን በእጅጉ መጣመሙን ያሳያል! በዚህ ጠማማ ሚዛን አቶ መለሰ ዜናዊ "ወርቅ ከሆነዉ የትግራይ ህዝብ በመወለዴ እኮራለሁ" ማለቱ እንዴት ሊነቀፍ ይችላል? የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ትክክለኛዉን ይረዳል!
በኢትዮጵያ ላይ ነግሶ ለ 27 ዓመታት ሀገርን እና ህዝብን እየጋጠ የነበረዉ የህወሀት ጁንታ 2010 ወደ መቀሌ ሸሽቷል! እንደሌላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የጁንታዉ ጭቆና ሰለባ የነበረዉ የትግራይ ህዝብ ደግሞ በወቅቱ ከለውጡ ጎን በመቆም ሌባዉን ጁንታ ከለላ መከልከሉም ይታወቃል! ነገር ግን የአማራ ፅንፈኛ በተለያዩ ቦታዎች ንፁኃን ትግራዋዮችን ከማጥቃቱ እና ወደ ትግራይ የሚገቡ መንገዶችን ከመዝጋቱ ባሻገር "ትግራይን እንጨብጣለን" ብሎ በመፎከሩ የትግራይ ህዝብ ለዉጡን ለመጠራጠር ተገዷል። ጁንታዉም "ለዉጡ ያነጣጠረዉ በህወሀት መሪዎች ሌብነት እና ኢሰበአዊነት ላይ ሳይሆን በትግራዋይነት ላይ ነዉ" ብሎ በመስበክ ከለላ ሊያገኝ ችሏል። በዚሁ ምክንያት በ 2010 ማለቅ ይችል የነበረዉ የህወሀት ጁንታ ዘመን እስከ ህዳር 2013 ተራዝሟል! ይህ የአማራ ፅንፈኛ ያልተገባ ባህሪ ኢትዮጵያዊያንን በአጠቃላይ እና አማሮችን ደግሞ በተለይ ያልተገባ ዋጋ አስከፍሏል!
አሁን አረመኔዉ የህወሀት ጁንታ ላይመለስ የመጨረሻዉ መጨረሻ ላይ ደርሷል! የአማራ ፅንፈኛ ደግሞ የጁንታዉ የሙት መንፈስ በትግራይ ላይ እንዲሰነብት እየሰራ ይገኛል! መጀመሪያ ነገር በትግሉ ህደት የተሰዉ ጀግኖች ሳይቀበሩ፣ በጁንታዉ የታፈኑ የህዝብ ልጆች ያሉበት ሁኔታ ሳይታወቅ እና የአረመኔዉ ጁንታ ስርዓተ ቀብር ሳይፈፀም ለመሬት ቅርምት ማሰፍሰፍ ቢያስ የጁንታዉ ፕሮፓጋንዳ ተሰሚነት እንዲያገኝ ይረዳል! እኩልነትን፣ ነፃነትን እና ወንድማማችነትን ከማራመድ ፈንታ አለማጣ ላይ ትግርኛ እና ኦሮምኛ ተናጋሪዎችን "አማራ ነን ብላችሁ ፈርሙ ወይም አከባቢዉን ልቀቁ" እየተባለ አማራነትን ለማጥመቅ የተያዘዉ ዘመቻ ከጁንታዉ ህወሀት በላይ ጁንታነት ይሆናል!
የታላቁን አማራ ስም ከማጉደፍ ባሻገር "እኔ ከሞትኩ ማንነትህን እና መሬትህን ትነጠቃለህ" የሚለዉን የጁንታዉን ትርክት ትክክል ያስመስላል! ድምር ዉጤቱ ደግሞ ከማንም በላይ አማራዉን ስለሚጎዳዉ ይህን ፅንፈኛ አካሄድ አጥብቆ የሚታገል አማራዉን ያጠቃል ሳይሆን አማራዉን ከጥቃት ይታደጋል!
እንደብልፅግና ፓርቲ ፅንፈኝነት የኢትዮጵያ ህልውና አደጋ መሆኑን በመስማማት በአንክሮ ለመታገል ወስነናል። ስለዚህ ፅንፈኝነትን በግላጭ የሚታገል የብልፅግና አባል ወይም አመራር ግዴታዉን በአግባቡ እየተወጣ ይገኛል! ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊያንም ጥብቅና ይቆማል! እዉነት እና ንጋት ደጎሞ እያደር ይጠራል!
እዉነቱን እንነጋገር!
ትላንት አንድ ተረት ሰምቼ እጅግ ገርሞኛል! ተረቱ " ታዬ ደንደአ እንደ ስባት ነጋ አማራን በነገር ለማጥቃት የተመደበ ባለጊዜ ነዉ" ይላል። ለካ በኢትዮጵያ የሀሰት ትርክት ሲደረት የነበረዉ በዚህ መልክ ኖሯል? ግን ከአሁን በኋላ ማን በድሮ በሬ ያርሳል? ብልፅግና እዉነቱን በማጋለጥ ለፍትህ ይሰራል!
የአንድ ማህበረሰብ ጠላት ከማህበረሰቡ የሚነሳዉ ፅንፈኛ ነዉ። በ2ኛ የዓለም ጦርነት ጀርመንን ያወደማት ራሺያ ወይም አሜሪካ ሳይሆን ፅንፈኛዉ ናዚ መሆኑ ምስክር የማያሻዉ ሀቅ ነዉ! ይህ ለሌሎች ማህበረሰቦችም ይሰራል! ለመሆኑ አማራን እያጠቃ ያለዉ ማነዉ? በኔ እይታ የአማራ ህዝብ ዋነኛ ጠላት በአማራ ስም የሚፎክረዉ ፅንፈኛ ነዉ! የአማራ ፅንፈኞች "አማራነት የሰዉነት ዉሃ ልክ ነዉ! የደቡብ ሰዉ የሚማረዉ አማራ ለመሆን ነዉ! አማራ ከየመን ስለመጣ ከሌላዉ ብሔር በላይ ነዉ! " ሲሉ አማራ በወንድሞቹ ዘንድ በጥርጣሬ እንዲታይ በማድረግ ዘመድ መስለዉ እያጠቁት መሆኑ ሊታወቅ ይገባል! የፅንፈኞቹን ናዚያዊ ፉከራ ሰምቶ ደስ የሚለዉ ወይም በግላጭ ለመቃወም የሚፈራዉ የአማራ ምሁር ወይም አመራርም አማራዉን ከማጥቃት አኳያ የድርሻዉን ይወስዳል! የኦሮሞ ፅንፈኞች " ሌላ ብሔር ያገባ ይፍታ! ዲቃላን እናጠፋለን! የጀግኖችን ደም እንበቀላለን! ነፍጠኛን ከኦሮሚያ እናባርራለን" ሲሉ ፊት ለፊት ገጥመን እና የህይወት ዋጋ ከፍለን በመታገል "የነፍጠኛ ተላላኪ" የተባልነዉ የስድብ ናፍቆት ኖሮብን ወይም የጓዶቻችን ህይወት ሳያሳዝነን ቀርቶ ሳይሆን በፅንፈኞች የወረደ ጀብደኝነት ኦሮሞ በወንድሞቹ ዘንድ ያለዉ ክብር እና ከፍታ እንዳይነካ ስንል መሆኑ ሁሉም ቢያዉቅ ይጠቅማል! የኦሮሞን ፅንፈኛ ስንታገል "ጀግና" እያለ ሲያወድሰን የነበረዉ ደግሞ ዛሬ የአማራ ፅንፈኛ ሲነካ "አካኪ ዘራፍ" ሲል ፍትህን የምንለካበት ሚዛን በእጅጉ መጣመሙን ያሳያል! በዚህ ጠማማ ሚዛን አቶ መለሰ ዜናዊ "ወርቅ ከሆነዉ የትግራይ ህዝብ በመወለዴ እኮራለሁ" ማለቱ እንዴት ሊነቀፍ ይችላል? የኢትዮጵያ ህዝብ ግን ትክክለኛዉን ይረዳል!
በኢትዮጵያ ላይ ነግሶ ለ 27 ዓመታት ሀገርን እና ህዝብን እየጋጠ የነበረዉ የህወሀት ጁንታ 2010 ወደ መቀሌ ሸሽቷል! እንደሌላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ የጁንታዉ ጭቆና ሰለባ የነበረዉ የትግራይ ህዝብ ደግሞ በወቅቱ ከለውጡ ጎን በመቆም ሌባዉን ጁንታ ከለላ መከልከሉም ይታወቃል! ነገር ግን የአማራ ፅንፈኛ በተለያዩ ቦታዎች ንፁኃን ትግራዋዮችን ከማጥቃቱ እና ወደ ትግራይ የሚገቡ መንገዶችን ከመዝጋቱ ባሻገር "ትግራይን እንጨብጣለን" ብሎ በመፎከሩ የትግራይ ህዝብ ለዉጡን ለመጠራጠር ተገዷል። ጁንታዉም "ለዉጡ ያነጣጠረዉ በህወሀት መሪዎች ሌብነት እና ኢሰበአዊነት ላይ ሳይሆን በትግራዋይነት ላይ ነዉ" ብሎ በመስበክ ከለላ ሊያገኝ ችሏል። በዚሁ ምክንያት በ 2010 ማለቅ ይችል የነበረዉ የህወሀት ጁንታ ዘመን እስከ ህዳር 2013 ተራዝሟል! ይህ የአማራ ፅንፈኛ ያልተገባ ባህሪ ኢትዮጵያዊያንን በአጠቃላይ እና አማሮችን ደግሞ በተለይ ያልተገባ ዋጋ አስከፍሏል!
አሁን አረመኔዉ የህወሀት ጁንታ ላይመለስ የመጨረሻዉ መጨረሻ ላይ ደርሷል! የአማራ ፅንፈኛ ደግሞ የጁንታዉ የሙት መንፈስ በትግራይ ላይ እንዲሰነብት እየሰራ ይገኛል! መጀመሪያ ነገር በትግሉ ህደት የተሰዉ ጀግኖች ሳይቀበሩ፣ በጁንታዉ የታፈኑ የህዝብ ልጆች ያሉበት ሁኔታ ሳይታወቅ እና የአረመኔዉ ጁንታ ስርዓተ ቀብር ሳይፈፀም ለመሬት ቅርምት ማሰፍሰፍ ቢያስ የጁንታዉ ፕሮፓጋንዳ ተሰሚነት እንዲያገኝ ይረዳል! እኩልነትን፣ ነፃነትን እና ወንድማማችነትን ከማራመድ ፈንታ አለማጣ ላይ ትግርኛ እና ኦሮምኛ ተናጋሪዎችን "አማራ ነን ብላችሁ ፈርሙ ወይም አከባቢዉን ልቀቁ" እየተባለ አማራነትን ለማጥመቅ የተያዘዉ ዘመቻ ከጁንታዉ ህወሀት በላይ ጁንታነት ይሆናል!
የታላቁን አማራ ስም ከማጉደፍ ባሻገር "እኔ ከሞትኩ ማንነትህን እና መሬትህን ትነጠቃለህ" የሚለዉን የጁንታዉን ትርክት ትክክል ያስመስላል! ድምር ዉጤቱ ደግሞ ከማንም በላይ አማራዉን ስለሚጎዳዉ ይህን ፅንፈኛ አካሄድ አጥብቆ የሚታገል አማራዉን ያጠቃል ሳይሆን አማራዉን ከጥቃት ይታደጋል!
እንደብልፅግና ፓርቲ ፅንፈኝነት የኢትዮጵያ ህልውና አደጋ መሆኑን በመስማማት በአንክሮ ለመታገል ወስነናል። ስለዚህ ፅንፈኝነትን በግላጭ የሚታገል የብልፅግና አባል ወይም አመራር ግዴታዉን በአግባቡ እየተወጣ ይገኛል! ለኢትዮጵያና ለኢትዮጵያዊያንም ጥብቅና ይቆማል! እዉነት እና ንጋት ደጎሞ እያደር ይጠራል!