ወያኔ የመጨረሻዋን ገመድ በጥሷል!
Posted: 02 Nov 2020, 09:31
ሁሉ ነገር በዲዛይን በእቅድ የሆነ ነው። ከቤንሻንጉል እስከጉራፈርዳ አሁን ደግሞ ወለጋ ጉሊሶ የሆነው በአጋጣሚ አልያም የተነጣጠሉ፣ ያልተያያዙ ክስተቶች አይደሉም። በወያኔ የመጨረሻ ዙር ሩጫ ውስጥ እንዲፈጸሙ በእቅድ የተያዙ ናቸው። ሌላው ቀርቶ በአፋርና ሶማሌ ክልሎች መሀል ይህን ጊዜ ጠብቆ የተነሳውና በርካታ ሰላማዊ ዜጎች እየተገደሉበት ያለው ግጭትም በዚሁ የወያኔ የመጨረሻ ዘመን እቅድ ውስጥ የሚገኝ ስለመሆኑ አያጠራጠርም።
አሁን ወያኔ በተኗን ነክቷል። የመጨረሻዋን ገመድ በጥሷል። ለዚህን ዘመን፣ ለመጨረሻው ሩጫው እዚህም እዚያም ያዘጋጀውን የጥፋት ሃይል አንቀሳቅሷል። ኢትዮጵያን እኛ ካልመራናት ትጥፋ የሚለው የወያኔ እርኩስ ቃልኪዳን በወያኔ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እውን የሚያደረግበት እርምጃ የተጀመረ ይመስላል። እንግዲህ ስጋ መሬት ላይ ወድቆ አፈር ለምን ይነካዋል አይባልም። ከጀመሩት በጥንቃቄና በብልሃት መግባት ነው። አማራጭ የለውም።
አሁን ወያኔ በተኗን ነክቷል። የመጨረሻዋን ገመድ በጥሷል። ለዚህን ዘመን፣ ለመጨረሻው ሩጫው እዚህም እዚያም ያዘጋጀውን የጥፋት ሃይል አንቀሳቅሷል። ኢትዮጵያን እኛ ካልመራናት ትጥፋ የሚለው የወያኔ እርኩስ ቃልኪዳን በወያኔ የጊዜ ሰሌዳ መሰረት እውን የሚያደረግበት እርምጃ የተጀመረ ይመስላል። እንግዲህ ስጋ መሬት ላይ ወድቆ አፈር ለምን ይነካዋል አይባልም። ከጀመሩት በጥንቃቄና በብልሃት መግባት ነው። አማራጭ የለውም።