Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Zmeselo
Senior Member+
Posts: 37344
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by Zmeselo » 22 Oct 2020, 23:39

ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡



ሰውዬውን አልቻሉትም፡፡ አፍነው ሊያጠፉት አስበው እንደጢስ በትንሽ ቀዳዳ ወጣና የሰማይ ስባሪ እስከሚመስል ገኖ ወጣባቸው፡፡ እንዳያሳንሱት ከህይወት በላይ ግዙፍ ነው፡፡ እንዳያሞግሱት ንቆ ስለተዋቸው እንዴት ይመስክሩለት፡፡ በዘመናዊ መልክ ሪፖርት አቀናጅተው እንዳይጽፉ ደሞ ለክፋቱ ሰዉዬው አይናገርም፡፡ እንዲያው የጨነቀ ነገር!

አንድ ሰው ለአንድ ወንጀል አንዴ ነው የሚቀጣው፡፡ ቅጣቱ ረጂም ወይም አጭር ሊሆን ይችላል፡፡ የኤርትራ መንግስት ወንጀለኞች ብሎ እጀ ከፍንጅ የያዛቸውን ሰዎች አስፈርዶ ቅጣታቸውን ስጥቷቸዋል፡፡ ሰዎቹ ፍ/ቤት እየተመላለሱ ችሎት ባይታደሙም፡ ፍርድ ቤቱ አሉበት ድረስ እየሄደ ወንጀላቸው ተነቦላቸው በአቃቤ ሕግ ክስ ተመስርቶባቸውና ማስረጃ ቀርቦ ፍርዳቸውን ተቀብለዋል፡፡

በኤሪ- ቶፒያ የሰላም ግኑኝነት ማግስት ለ20 አመታት ታስሮ የተፈታው፡ የትግሬው ሰላይ ጋዜጠኛ ለትግርኛው ቪኦኤ ቀርቦ ሲያስረዳ፡ በ1998 ጦርነት ወቅት ከትግራይ ወደ ኤርትራ ስለሄድኩ ነው የታሰርኩት አለ፡፡ ለምን ሄድክ ሲባል?
ኤርትራ ውስጥ ነው ተወልጄ ነው ያደኩትና አብሮ አደጎቼን ልጠይቅ ነበር የሄድኩት ሰላይ ነህ ተብዬ ተያዝኩ
አለ፡፡

እንግዲህ ኤርትራ ነጻነቷን ስታገኝ ኢትዮጵያዊ ነኝ ብሎ አገሩ የተመለሰ ትግሬ የወያኔ ጋዜጠኛ ነው፡፡ በጦርነቱ አካባቢ ሲመለስ ተይዞ የ20 አመት እስር ተፈረደበት፡፡ እሱ
ጓደኞቼን ልጠይቅ ነው የመጣሁት ንጹህ ሰው ነኝ፡፡
የኤርትራ መንግስት ደሞ
የለም ወሬ ልትለቃቅሚ ነው የመጣሺው የወያኔ ተላላኪ ነሸ አለቅሽም
ብሎ አሰረው፡፡

እነሱ መሃል ገብተን ለመፍረድ ስለሚያዳግት እርስ በርስ ይተዋወቃሉ ብለን ነገሩን እንተወዉና ስሙን ያልያዝኩት ትግሬው ጋዜጠኛ የእስር አያያዙ እንዴት እንደነበር ሲጠየቅ፡ ለቀረበብኝ ክስ ሂደቱ እስኪጠናቀቅ ጊዜያዊ ፍ/ቤት እስር ቤት ይቋቋማል፡፡ በዛ መሰረት እስረኛ ፍርዱን እዚያው ይቀበላል፡፡ በዛው እስሩ ይቀጥላል፡፡ አንዴ ፍርዴን ካገኘሁ በኋላ ግን ትምህርት እንድማር ተደርጎ ትምህርቴን ስጨርስ እንዳስተምር ተደርጌ ስለነበር የባከነ ሕይወት የለኝም፡፡ በተለይ ከቤተሰብ ተለይቼ የመኖር ክብደቱን አቃሎልኛል፡፡ ሲል መለሰ፡፡ ጠያቂዋ ግና በመልሱ አልረካችም፡፡ አሰቃዩኝ፤ ገረፉኝ፤ እጅግ አስቃቂ ኑሮ አለፍኩኝ እንዲላት ብዙ ወተወተችው፡፡ ለፖለቲካ ፍጆታ ብሎ የተሰጠውን ክብር ሊሸሽግ አልቻለም፡፡

መዋሸት ቢፈልግም ሊዋሽ አይችልም፡፡ ቅንድቡን ሳይቀር አንብበው እንደቀነደቡት ያቃል፡፡ ዋጋ ከፍሎ ነው የወጣው፡፤ አጉል ለፖለቲካ ብሎ ቢዘባርቅ የኤርትራ ደህንነት ኪሱ ውስጥ እንዳለም ይረዳል፡፡ (ምንጭ ቪ ኦ ኤ ትግርኛው ክፍል)

እንግዲህ ይህን የእስር አያያዝ ነው በየአመቱ
የሰብአዊ መብት አያያዝ
እየተባለ ፊት እየተነጨ የሚለቀስላቸው፡፡

ቢቀናቸው እኮ አገራችንን ለወያኔ ሊያስረክቡልን ሲሞዳሞዱ የነበሩ ራስ ወዳድ ወንጀለኞችን ነው መንግስትን ለምን አስርክ እየተባለ ከትግራይ እስከ አዉሮፓ የናኘ ጩኸት የሚሰማው፡፡

እውነቱን ገልጠን ስናየው ግን በግልጽ ወንጀል የሚታወቁና ከራሳቸው ተከፍለው ስልጣን ሊይዙ የፈለጉ 15 ሰዎች አሉ፡፡ ከነሱ ስር ሆነው ኩዴታውን ለማጧጧፍ ሲበረቱ የተያዙ 16 ጋዜጠኞች አሉ፡፡ ከ16ቱ ውስጥ አንዱ የስዊድን ዜግነት ያለው ሰላይ ነው፡፡ ልክ እነደ ወረቀት በኮፒ ማሽን አባዝተው ስለነሱ ሲወራ እውነትም ይህን ሰዉዬ በምላስ እንጂ በጉልበት እንደማይችሉት ያስረዳል፡፡ ምነው ዘገምተኛው መስፍን ባለቀ ሰአት ትግራይ ሄጄ ሰራዊት እመሰርታለሁ ሲል ጉዳቸው ብዙ እንደሆነ አይነግረንም? ይልቁንስ ዘገምተኛውን መስፍን
ትግራዮ በአንበጣና በረሃብ ተጎድታለች ሰራዊትህን ምን እያበላህ ልታዋጋ ነው?
በሉት፡፡

ቢያንስ የበላውን ገንዘብ ይመልስ፡፡ ተዋግቶ ላይዋጋ የትግሬ ድሃውን አጉል ጎዱት፡፡

እርግጥ ነው ፍርድ ቤቱን ለምን እስር ቤት ወሰዳችሁት ብሎ መጠየቅ የአባት ነው፡፡ በአገሪቱ ህልውና ላይ ቁማር አስይዘው ሲጫወቱ የተገኙትን ለምን ተበላችሁ ብሎ ቁጭት ግን ሌላ ታሪክ ነው፡፡ ከዳር ሆነን ስንመለከተው፡ G15 ቢያሸንፉ ኖሮ የቀሩት ደሞ ለምን ታሰሩ ብለን ሙሾ እንወርድ ነበር ይሆን? አንዲት ሏአላዊት ሃገር ወንጀለኞቿን መያዝ፤ ድንበሯን ለመጠበቅ ወታደሮቿን ማሰልጠን፤ ከውጪ ጣልቃ ገብነት የሚቆጣጠር የደህንነት መዋቅሯን ማዘመን ተገቢና ግዴታ ነው፡፡ እንደ ድንገት ሆኖ የምንወዳቸው ሰዎች እዚህ ቁማር ገበተው ለመብላት ሲያስቡ ተበልተው እንደሆነ፡ የጨዋታው ሕግ ነው፡፡ ወይ ትበላለህ ወይ ትበላለህ፡፡ ሰባዊ መብት የሚል ውሽት አላብሶ ማለቃቀስ ግና ሰውየውን አልቻልነውምና ዛሬ ደሞ ምን ብለን ስሙን እናጥፋ ''አቅሊ ጽበት'' ነው፡፡

የሰውየው ሰራዊት በአውሮፓ ተበትኖ 4ኛ ጉባኤ ስልጠናና ምክክር ሲያደርግ መክረሙ ሳያስደነግጣቸው አልቀረም፡፡ የወጣት ክንፉም በኮቪድ 19 ምክኒያት ተቋርጦ የቆየውን ስብሰባና ሴሚናር ቀጥሏል፡፡ ሻዕቢያ ውስጥ ውስጡን ያሰለጠናቸው ብዛታቸውን መድሃኒያለም ይቁጠረው፡፡ ስልጣን ፈላጊው አፉ ውሃ እንደሞላ እንደ እሳት የሚነዱ ትውልዱን እየተካ ነው፡ በአንድ ሰው ተደጋጋሚ ክስ ማቅረብና መወንጀል ውስጠ ወይራ ብሽቀት ነው፡፡ ይሄኔ እኮ ዳዊት ይስሃቅን ቅልጥ ያለ ካድሬ ድርገውት ይሆናል፡፡ አለበለዚያም ጥፋቱን አምኖ ተናዞ ይሆናል፡፡ ያ የትግሬ ጋዜጠኛ የራሱን ምስክርነት እንደሰጠው፡ ጥሩ መምህር አድርገውትም ይሆናል፡፡

በቢልዮኖች ተበጅቶ ህልቁ መሳፍርት ሰዎች አሰልጥነውና 10 አገራት ተባብረው መጣል ሲያቅታቸው፡ አንጀታችን አረረ፤ ከሰርን እንዴት ይበሉ፡፡ በእውነቱ ወንድነትን የሚፈታተን አንዳች ዱብ እዳ አወረደባቸውና ምላሳቸውን ዘርግተው ሲሳደቡ ይውላሉ፡፡ አወይ ቅሌት፡፡

ሰዉዬም የኮቪድን ህግ እየደረማመሰ አፍሪካንና መካከለኛውን ምስራቅ ፖለቲካ ሰጥ ለጥ አድርጎ ይመራል፡፡ የቀይ ባህር ከባቢ እንዴት እንደሚጠበቅ ረቂቁን ጽፎ አስረክቧል፡፡ ከሱ ፈቃድ ውጪ የሚሰራም የማይሰራም የለ፡፡ ሰውየውን አለማድነቅ አይቻልም፡፡ ፊት የነሳቸው ሲረበሹ፤ ፊት የሰጣቸው ሲቦርቁ፤ የተሸነፉ ሲያጠለሹት አይተናል፡፡ ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም፡፡

ጌም ኦቨር ሲላቸው ያልገባቸው የደደቢት ደደቦች፡ በሽምግልናቸው ወቅት አንበጣ በእንጨት ሊያባርሩ ከሰፈር ሰፈር ይሯራጣሉ፡፡ የኢትዮጵያም መንግስት ከአንበጣ ወግኖ አንበጣውን አስጣጥቆታል መሰለኝ፡ የትግሬ ጀግኖች ''ወይ ፈተኽ" እያሉ አቀባብለው እየተኮሱ ነው፡፡ ሰዉዬው እጁን ኪሱ ከቶ በተመደበለት ልዩ የሮያል ጄት የአለም መናኸሪያ የሆነችውን የቀይ ባህር ጂኦፖለቲክስ እንደባህር ወጀብ ሲንጣት ይውላል፡፡

ቪቫ ሻዕቢያ!!!
ዓወት ንሓፋሽ!!!

(C/o Meadi Guasot)


_______________






Last edited by Zmeselo on 23 Oct 2020, 18:26, edited 5 times in total.

Zmeselo
Senior Member+
Posts: 37344
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by Zmeselo » 22 Oct 2020, 23:51

The COVID19 pandemic has disrupted the economic growth of many countries (wealthy or not) and if these IMF growth projections are any indication, Eritrea's projected 3.8% growth for 2019 will be contracted to (-0.6%) next year before it bounces back to a promising 5.7% in 2021; provided nothing stupid (politically or economically) happens in between. (Click image to enlarge)



______________




(VOA) — ኣብ ምህዞን ሰንዓን ዝነጥፍ መንእሰይ መሃንድስ ኣሕፈሮም ተኸስተ መቐጸልታ ናይ’ቲ ቅድሚ ሕጂ ዝሰርሖም ናይ ምህዞን ሰንዓን ስርሓት፡ ኣብ መስርሕ ምቁጽጻር ምንፋር ዘይጀመሩ ዕስለ ኣንበጣ ዝውዕል ማሽን ስኒዑ’ሎ።

እታ ማሽን ብዘይ ጸዓት ትሰርሕ ኮይና ኣብ ጽሬት ሆስፒታላትን ጎደናታትን’ውን ከምእተገልግል መሃንድስ ኣሕፈሮም ንድምጺ ኣሜሪካ ተዛሪቡ።

ምሉእ ትሕዝቶ ኣብዚ ምስማዕ ይክኣል >> https://av.voanews.com/clips/VTG/2020/1 ... e2_16k.mp3

Zmeselo
Senior Member+
Posts: 37344
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by Zmeselo » 23 Oct 2020, 10:06





#EritreaGraduationSeason: College of Engineering & Technology conferred 1st Degrees to 129 & Diplomas to 237 Graduates in Chemical, Computer, Civil, Electrical, Electronics, Mining & Marine Engineering in its 13th Commencement today held in the New Normal of standard virtual format. ኮሌጅ ምህንድስናን ቴክኖሎጅን፡ ላዕለዎት ትካላት ትምህርቲ ቅጥዕታት ምክልኻል ‘ኮቪድ 19’ ተኸቲለን ብመሰረት ዘካይድኦ ዘለዋ ስነ-ስርዓት መመረቕታ፡ ሎሚ 23 ጥቅምቲ፡ ኣብ መበል 13 ዙርያ 129 ብዲግሪ፡ 237 ድማ ብዲፕሎማ ብጠቕላላ 366 ተመሃሮ ኣመሪቑ። ምሩቓት፡ ብምህንድስና ስነ-ቀመም፡ ምህንድስና ኮምፕዩተር፡ ምህንድስና ስነ-ህንጻ፡ ምህንድስና ኤለክትሪክን ኤለክትሮኒክስን፡ መካኒካዊ ምህንድስና፡ ምህንድስና ዕደና፡ ከምኡ’ውን ምህንድስና ስነ-ባሕሪ’ዮም ትምህርቶም ዛዚሞም።
(Yemane G. Meskel: @hawelti)


Last edited by Zmeselo on 23 Oct 2020, 18:33, edited 4 times in total.

Zmeselo
Senior Member+
Posts: 37344
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by Zmeselo » 23 Oct 2020, 10:16

መዘክር ታሪኽ - ሓሬና ክነግረኪ እቲ ምስጢሩ ፣ ዛንታ ኣቦኺ ክትኮርዕሉ - DimTsi Hafash Eritrea/ድምጺ ሓፋሽ ኤርትራ





Embassy Media Special Broadcast 21 Nov.–15 Dec. 2020 'Warsay–The Pride of Three Generations'


Zmeselo
Senior Member+
Posts: 37344
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by Zmeselo » 23 Oct 2020, 10:53










Eritrea local markets & handcrafted local products.
(ኤርትራ ERITREA: @thedrosg1)

_______________


Asmara, in the 1960s.
Last edited by Zmeselo on 23 Oct 2020, 19:18, edited 3 times in total.

Zmeselo
Senior Member+
Posts: 37344
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by Zmeselo » 23 Oct 2020, 11:13



_____________


Selection of historical Eritrean stamps, focusing on Eritrea's incredibly diverse and beautiful wild life. Via US Embassy in Asmara

Zmeselo
Senior Member+
Posts: 37344
Joined: 30 Jul 2010, 20:43

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by Zmeselo » 23 Oct 2020, 13:52





Signing of the poster- Eritrea reaffirming commitment 2 multilateralism-and upholding the ⁦#UNCharter. At 75, while much has been accomplished by @UN, there remains even more 2 B done 2 live up to the aspirations of peoples living everywhere-rich or poor, small or big.
(Amb. Sophia Tesfamariam: @stesfamariam)

quindibu
Member
Posts: 3279
Joined: 31 Dec 2010, 13:17

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by quindibu » 23 Oct 2020, 15:59

ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡



Well written and humorous!
ሰውዬውን አልቻሉትም፡፡ አፍነው ሊያጠፉት አስበው እንደጢስ በትንሽ ቀዳዳ ወጣና የሰማይ ስባሪ እስከሚመስል ገኖ ወጣባቸው፡፡ እንዳያሳንሱት ከህይወት በላይ ግዙፍ ነው፡፡ እንዳያሞግሱት ንቆ ስለተዋቸው እንዴት ይመስክሩለት፡፡ በዘመናዊ መልክ ሪፖርት አቀናጅተው እንዳይጽፉ ደሞ ለክፋቱ ሰዉዬው አይናገርም፡፡ እንዲያው የጨነቀ ነገር!

በቢልዮኖች ተበጅቶ ህልቁ መሳፍርት ሰዎች አሰልጥነውና 10 አገራት ተባብረው መጣል ሲያቅታቸው፡ አንጀታችን አረረ፤ ከሰርን እንዴት ይበሉ፡፡ በእውነቱ ወንድነትን የሚፈታተን አንዳች ዱብ እዳ አወረደባቸውና ምላሳቸውን ዘርግተው ሲሳደቡ ይውላሉ፡፡ አወይ ቅሌት፡፡
ሰዉዬም የኮቪድን ህግ እየደረማመሰ አፍሪካንና መካከለኛውን ምስራቅ ፖለቲካ ሰጥ ለጥ አድርጎ ይመራል፡፡ የቀይ ባህር ከባቢ እንዴት እንደሚጠበቅ ረቂቁን ጽፎ አስረክቧል፡፡ ከሱ ፈቃድ ውጪ የሚሰራም የማይሰራም የለ፡፡ ሰውየውን አለማድነቅ አይቻልም፡፡ ፊት የነሳቸው ሲረበሹ፤ ፊት የሰጣቸው ሲቦርቁ፤ የተሸነፉ ሲያጠለሹት አይተናል፡፡ ይታደሉታል እንጂ አይታገሉትም፡፡
[]i]ጌም ኦቨር[/i] ሲላቸው ያልገባቸው የደደቢት ደደቦች፡ በሽምግልናቸው ወቅት አንበጣ በእንጨት ሊያባርሩ ከሰፈር ሰፈር ይሯራጣሉ፡፡ የኢትዮጵያም መንግስት ከአንበጣ ወግኖ አንበጣውን አስጣጥቆታል መሰለኝ፡ የትግሬ ጀግኖች ''ወይ ፈተኽ" እያሉ አቀባብለው እየተኮሱ ነው፡፡ ሰዉዬው እጁን ኪሱ ከቶ በተመደበለት ልዩ የሮያል ጄት የአለም መናኸሪያ የሆነችውን የቀይ ባህር ጂኦፖለቲክስ እንደባህር ወጀብ ሲንጣት ይውላል፡፡




[/quote]

( ͡° ͜ʖ ͡°)
Member
Posts: 2312
Joined: 11 Jan 2020, 21:22

Re: ጉልበት ሲያጥር ምላስ ይረዝማል፡፡

Post by ( ͡° ͜ʖ ͡°) » 23 Oct 2020, 18:10

:P :P :P :P
I enjoyed reading the article. It is great!



Post Reply