Page 1 of 1

አፍሮ ባሮሜትር በኢትዮጵያ ላይ ያወጣው ሰርቬይ ምን ይላል?

Posted: 27 Aug 2020, 23:45
by Horus
በ 3 ነገሮች ላይ ግልጽ ማጆሪቲ አለ፤
የጠ/ሚ ዘመን በ2 ምርጫ ይቁም
የፌዴራል ቋንቋዎች ይብዙ
ራሱን የቻለ የሕግ መንግስት ፍርድ ቤት ይቁም

በቀሩት ላይ ሁሉ በመሰረቱ ሕዝብ ግማሽ ላይ ተከፋፍሏል
አዲስ አበባ የራሱ እስቴት ይሁን
አንቀጽ 39 ይውጣ
ኮከቡ ከባንዲራው ይውጣ
መሬት ለግል ይሸጥ

የጥናቱ ሳይንሳዊነት ማን ያህል እንደ ሆነ አላቅም

https://afrobarometer.org/media-briefin ... nstitution

Re: አፍሮ ባሮሜትር በኢትዮጵያ ላይ ያወጣው ሰርቬይ ምን ይላል?

Posted: 28 Aug 2020, 19:01
by Horus
ይህ ሰርቬይ ትክክል ነው ብለን ብንነሳ ለዚህ አይነት የህዝብ አቋም ሑኔት ምን አይነት መፍትሄ ነው ማቅረብ ያለብን

1 የጠ/ሚ ወይም ፕሬዚዳንት ግዜ 2 ተርም ማድረግ ከ8 እስከ 10 አመት
2 ሁለት ወይም ሶስት ፌደራል ቋንቋ ማድረግ
3 ራሱን ያቻለ የሕገ መንግስት ፍርድ ቤት ማቆም
4 ክልል መባል ሳይሆን ራስ ገዝ ከተማ ማድረግ
5 አንቀጽ 39ን ወደ አገርነት እንዳይሄድ አንቀጽ ማስገባት ማለትም 39 ከራስ ገዝነት እንዳያልፍ ማድረግ
6 ሁለቱም ባንዲራዎች ህጋዊ ማድረኛ ሰው የፈለገውን እንዲያውለበልብ መፍቀድ
7 የተወኑ የመሬት አይነቶች እንዲሸጡ ሌልሎች ብኪራይ እንዶያዙ ማድረግ


በቃ !