Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 36342
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

አስታ ላቪስታ ታከለ ኡማ !! የሚቀጥለው ሺመልስ አብዲሳ ነው

Post by Horus » 18 Aug 2020, 10:07

አቢይ አህመድ ቀስ በቀስ መቆሚያ መሰረቱን ከጎሳ ካድሬዎች ወደ ክህሎታዊ ቴክኖክራቶች እያዞረ ነው !ኤቦ ያሰኛል የሚገርመው ነገር ግን አቢይ ይህን ነገር ለምን በ12 12 12 አውጀው የሚለው ነው!!
Last edited by Horus on 18 Aug 2020, 10:35, edited 2 times in total.


kolfe
Member
Posts: 57
Joined: 08 Apr 2013, 13:03

Re: አስታ ላቪስታ ታከለ ኡማ !! የሚቀጥለው ሺመልስ አብዲሳ ነው

Post by kolfe » 18 Aug 2020, 10:48

Horus,
What is the difference between Takele and a corrrupted Adanech Abebee? abo atasiqen….

Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4380
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: አስታ ላቪስታ ታከለ ኡማ !! የሚቀጥለው ሺመልስ አብዲሳ ነው

Post by Za-Ilmaknun » 18 Aug 2020, 12:11

Adanech Abebe....the presumptive Mayor of Addis Ababa! The demographic change will be on a steroids! :mrgreen: A City that has never been allowed to be administered by one of its own. Talk about self administration :lol: :mrgreen:

Horus
Senior Member+
Posts: 36342
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አስታ ላቪስታ ታከለ ኡማ !! የሚቀጥለው ሺመልስ አብዲሳ ነው

Post by Horus » 18 Aug 2020, 14:25

ኮልፌ፤
ምን ግዜም ቢሆን አንድን የስልጣን ቦታ አንተ አስካልያዝከው ድረስ በነገሩ ላይ ወስኝነት የለህም። ስለዚህ ባልያዝነው ስልጣን ላይ የኛን ፍላጎት የሚያስፈጽም የለም። ይህን አለማወቅ ትልቅ የዋህነት ነው። ታከለን የሾመው የኦሮሞ ፓርቲ ነው ።ታከለን ያነሳው የኦሮሞ ፓርቲ ነው። አዳነችንም እንዲሁ!

ትልቁ ጥያቄ ለምን ብለህ ጠይቅ? ለምንድን ነው በዚህ ሰዓት ታከለ የተነሳው? አዳነች ለምንድን ነው ካቃቤ ህጉ የተነሳቸው? እነዚህ ጥያቄዎች አስፈላጊ የሚሆኑት በሚከተለው ሎጂክ ምክኛት ነው።

አንደኛ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ የሆኑ ፖለቲከኞች የሚያጣላቸው ወይም አንድ የሚያደርጋቸው ነገር (1) ስልጣን፣ (2) ገንዘብ፣ (3) አማለካከት፣ ወይም (4) ማንነት/ዝና ነው ። ስለዚህ ታከለ ካቢይ ጋር ያለውን ችግር ከነዚህ 4 ነገሮች ታገኝዋለህ ። ያ ደሞ አቢይ ምን ላይ እንደ ቆመ፣ ምን ማድረግ እንዳለመ ይነግርሃል ። የታከለ መባረር ትልቅ ኢፎርሚውሽን ነው ለህዝቡ።

ሌላው ትልቁ ነገር የፖለቲካ ከረምቦላው ነው ። የፖለቲካ ዳይናሚክስ ልክ እንደ ክሮምቦላ ጠጠር ነው ። አንዱን ስትመታው ሁሉም ይነቃነቃል ። ይህ ሁሉ የምናየው ሹም ሽር በፒፒ ውስጥ ያለ መታመስ፣ የኦሮምው እልቂት፣ የነጃዋር መሸነፍ፣ አቢይ እያደረገ ያለው ጽዳት አካልና ሂደት ነው።

ልብ በል አዲስ አበባ የታከለ ከተማ አይደለችም፣ ያቢይ ከተማ ነች ፣ አዲሳባ የኢትዮጵያ እምብርት ነች ። ታከለ የተነሳው አዲስ አበባን አቢይ በፈልገው መንገድ ማስተዳደር ስላልቻለ ነው ። ነገ አዳነች ትምጣ፣ ከበደ ይምጣ የሚሆነው ያ ነው።

ስለዚህ ጥያቄው አዳነች አቤቤ ምን ትፈልጋለች አይደለም ። አቢይ አህመድ አዲስ አበባን እንዴት ነው ማስተዳደር የሚፈልገው የሚለው ነው ። ዛሬ አዲስ አበባ በፒፒ ስር ነው ያለው ። ፒፒ ደም ኦሮሞ ነው ሚነዳው። ስለዚህ አዲሳባ ራሱን እንዲገዛ መታገል ነው የህዝቡን ፍላጎት የሚያነግሰው ። በፒፒ ውስጥ ያለው ፍትጊያ ግን ለህዝቡ ትግል ግብዓትነት አለው፣ ፖለቲከኛ ከሆንክ ማለት ነው።

እስቲ ለማንኛውም ኢዜማ ይፋ የሚያደርገውን የመሬት ወረራ ከዚህ ጋር እንዴት እንደ ሚያያዝ ለማየት ያብቃን ። በእኔ ግምት በትክክል የተያያዘ ይምሰለኛል። ያዳነች መነሳት ግን ከነጃዋር ጋር ባላት የድሮ ቅርበት ይመስለኛል ። ሙሉ ቀን የምንሠማው የዚያ ገዳይ ጃዋር ድራማ ነው። አቢይ ቋቅ ያለው ይምስለኛል ። ስለዚህ በዚህ አንገብጋቢ 10 ሺ ሰዎች ክስ ወቅት የሷ መነሳት ሹም ሽር እንጂ ሹም ሹመት አይደለም ።

ለጊዜው ማባበያ እንጅ አዳነቸው ዘላቂ ከንቲባ አትሆንም ። አንድ አመት ብትቆይ ነው፣ እስከ ምርጫው ።

Horus
Senior Member+
Posts: 36342
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አስታ ላቪስታ ታከለ ኡማ !! የሚቀጥለው ሺመልስ አብዲሳ ነው

Post by Horus » 18 Aug 2020, 15:14

ኢትዮ360ች ግን ሺመልስ አብዲሳ ባሸናፊነት ወጥቷል የሚል ነው እይታቸው ። በኦሮሞ ፒፒ ውስጥ ያለው የስልጣን ትግል የሚወሰነው ይሆናል ። በዚህ ሁሉ ላይ አንድ አመለከከት የነኢትዮ360 ስለሆነ እነሆ


Horus
Senior Member+
Posts: 36342
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አስታ ላቪስታ ታከለ ኡማ !! የሚቀጥለው ሺመልስ አብዲሳ ነው

Post by Horus » 18 Aug 2020, 15:31

ታከለ የተነሳው የመሬት ውረራውን ለመሽፈን እና እሱን ለማዳን ይሆን?



Horus
Senior Member+
Posts: 36342
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

Re: አስታ ላቪስታ ታከለ ኡማ !! የሚቀጥለው ሺመልስ አብዲሳ ነው

Post by Horus » 24 Aug 2020, 13:31

ፒፒ ፓርቲ ግምገማ ተቀምጧል። በዚህ ግምገማ ሺመልስ አብዲሳን አለማውረድ ማለት የኦሮማራ መፍረስ ማለት ነው ። ያ ደሞ ለኢትዮጵያ ትልቅ እድል ነው ። ኢትዮጵያ ከማንኝውም የጎሳ ጥርቃሞ አምባገነንነት መላቀቅ አለባት ።

Post Reply