ምክር ቢጤ ለኢትዮጵያዉያን አርቲስቶችና የጥበብ ሰዎች በሙሉ
Posted: 03 Jul 2020, 04:53
አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ ኢትዮጵያዊው ወንድማችሁ፡ በጥበቡና በወኔው ግፈኞችን ፊት ለፊት ተጋፍጦ እርቃናቸውን ያወጣ ድንቅ የኦሮሞና የኦሮምያ ተወላጅ፡ ወጣት የልጆች አባትና ከልቡ በፈለቀ ፍቅር በዓላማ ጽናት በመታገል፡ ለዘመናት በህዝብ ጫንቃ ላይ ሲንፈላሰስ የነበረን አረመኒያዊ ስርዓት በመገርሰስ ጉልህ ሚና ያበረከተ ብርቅና ድንቅ የአንቦ ልጅ ነው።
ይህ ለጋ ወጣት መድረክ ላይ እንደ አንበሳ እየተጎማለለ የጥበብን ኃያልነትና የዜጎችን እኩልነት በድፍረት ገልጾ የጨለማ ኃይሎችን ዳግም እንዳያንሰራሩ አድርጎ ቀልባቸውን ስለገፈፈው፡ ነብሰበላዎቹ ህይወቱን ቀጥፈውታል። የኦሮምያ ክልላዊ መንግስትም የዚህን የጥበብ ሰው አኩሪ ታሪኩንና ገድሉን ይበልጥ ለመግለጥና ለዘመናት ተሻጋሪ በሆነ መልኩ ለትውልድ ለማስተላለፍ በአዲስ አበባ ሀውልት እንደሚያቆምለት ሰምተናል። የጨለማ ኃይሎችን ተንኮልና ሴራ እየገለጸ ለዘመናትና ለትውልድ እያስተላለፈ የሚኖር በጎ ግሩምና ክቡር ተግባርም ነው።
ኢትዮጵያዉያን የጥበብ ሰዎች ባጠቃላይ በተለይም ተመሳሳይ ድፍረትና የትግል ወኔ የዓላማ ጽናትና ቁርጠኝነት ያላችሁ እነ ቴዲ አፍሮና እነ ወዘተ እንዲሁም የአርትስ ቲቪዎቹ ጦቢያን በጃዝና ወዘተዎች ማለትም ተመሳሳይ ዝግጅቶች ጭምር፣ የጥበብን ኃያልነትና ባፈለቀው ልዩ የጥበብ ተሰጥኦው ምክንያት መስዋእት የሆነውን ኢትዮጵያዊ ወንድማችሁን ሀጫሉ ሁንዴሳንና ጥበብን ለማክበር፡ እንዲሁም ተስፋ የቆረጡ የጨለማ ኃይሎችን እኩይ ተግባር ይበልጥ ለማጋለጥ፡ አምላክ በጥበቡ በሰጣችሁ ተሰጥኦ ተጠቅማቹ፡ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ግሩም ኢትዮጵያዊ ሙዚቃ (እንጉርጉሮ) ለአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳና ተመሳሳይ ታሪክ ላላቸው ኢትዮጵያዉያን በሙሉ ታሪካዊ ግጥምና ዜማ ስሩለት እስቲ።
ኢትዮጵያዉያን የጥበብ ሰዎች ኢትዮጵያዊውን የጥበብ ሰው ሀጫሉ ሁንዴሳን ዘክሩት፤ ኣዎ ያኔ የኢትዮጵያዉያን አርቲስቶች ኢትዮጵያዊ ህብረዜማና ቅላጼ ቅኔና እንጉርጉሮ ከዳርእስከዳር ሲያስተጋባባቸው ግዜ የቃኤል መንፈስ የተጠናወታቸው የጨለማው የጥፋት ኃይሎች ይበልጥ ጨርቃቸውን ጥለው እርቃናቸውን ወጥትው እርማቸውን ያወጣሉና! በጨለማውና የጥፋት ኃይሎች መቃብር ላይም ኢትዮጵያ በሰላማዊው የእድገት ጎዳና ይበልጥ ትረማመዳለችና!
ክብርና ሞገስ ለድንቁ ኢትዮጵያዊ አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ!
ይህ ለጋ ወጣት መድረክ ላይ እንደ አንበሳ እየተጎማለለ የጥበብን ኃያልነትና የዜጎችን እኩልነት በድፍረት ገልጾ የጨለማ ኃይሎችን ዳግም እንዳያንሰራሩ አድርጎ ቀልባቸውን ስለገፈፈው፡ ነብሰበላዎቹ ህይወቱን ቀጥፈውታል። የኦሮምያ ክልላዊ መንግስትም የዚህን የጥበብ ሰው አኩሪ ታሪኩንና ገድሉን ይበልጥ ለመግለጥና ለዘመናት ተሻጋሪ በሆነ መልኩ ለትውልድ ለማስተላለፍ በአዲስ አበባ ሀውልት እንደሚያቆምለት ሰምተናል። የጨለማ ኃይሎችን ተንኮልና ሴራ እየገለጸ ለዘመናትና ለትውልድ እያስተላለፈ የሚኖር በጎ ግሩምና ክቡር ተግባርም ነው።
ኢትዮጵያዉያን የጥበብ ሰዎች ባጠቃላይ በተለይም ተመሳሳይ ድፍረትና የትግል ወኔ የዓላማ ጽናትና ቁርጠኝነት ያላችሁ እነ ቴዲ አፍሮና እነ ወዘተ እንዲሁም የአርትስ ቲቪዎቹ ጦቢያን በጃዝና ወዘተዎች ማለትም ተመሳሳይ ዝግጅቶች ጭምር፣ የጥበብን ኃያልነትና ባፈለቀው ልዩ የጥበብ ተሰጥኦው ምክንያት መስዋእት የሆነውን ኢትዮጵያዊ ወንድማችሁን ሀጫሉ ሁንዴሳንና ጥበብን ለማክበር፡ እንዲሁም ተስፋ የቆረጡ የጨለማ ኃይሎችን እኩይ ተግባር ይበልጥ ለማጋለጥ፡ አምላክ በጥበቡ በሰጣችሁ ተሰጥኦ ተጠቅማቹ፡ ከትውልድ ወደ ትውልድ የሚተላለፍ ግሩም ኢትዮጵያዊ ሙዚቃ (እንጉርጉሮ) ለአርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳና ተመሳሳይ ታሪክ ላላቸው ኢትዮጵያዉያን በሙሉ ታሪካዊ ግጥምና ዜማ ስሩለት እስቲ።
ኢትዮጵያዉያን የጥበብ ሰዎች ኢትዮጵያዊውን የጥበብ ሰው ሀጫሉ ሁንዴሳን ዘክሩት፤ ኣዎ ያኔ የኢትዮጵያዉያን አርቲስቶች ኢትዮጵያዊ ህብረዜማና ቅላጼ ቅኔና እንጉርጉሮ ከዳርእስከዳር ሲያስተጋባባቸው ግዜ የቃኤል መንፈስ የተጠናወታቸው የጨለማው የጥፋት ኃይሎች ይበልጥ ጨርቃቸውን ጥለው እርቃናቸውን ወጥትው እርማቸውን ያወጣሉና! በጨለማውና የጥፋት ኃይሎች መቃብር ላይም ኢትዮጵያ በሰላማዊው የእድገት ጎዳና ይበልጥ ትረማመዳለችና!
ክብርና ሞገስ ለድንቁ ኢትዮጵያዊ አርቲስት ሀጫሉ ሁንዴሳ!