አስደንጋጭ ነው!!
Posted: 26 Apr 2020, 16:19
ሃቅ፣ ፍትህና ሰላም ወዳዱ የትግራይ ህዝብ የህወሓት መሪዎችን በሰላማዊና በሰለጠነ መንገድ ቁጭ አድርጎ መገምገምና መጠየቅ እንደሚጀምር መላው የኢትዮጵያ ህዝብ የሚጠብቀው ክስተት ነው፤ ይህ ስልጡን የታሪክ ክስተት እንዲፈፀምም በአንዳንድ ሃላፊነት የጎደላቸው አካላት ይፈጠሩ የነበሩ ተንኳሽ አጀንዳዎች እንዲቆሙ ስንወተውት ቆይተናል። ሆኖም ግን ህዝባችን በቅርቡ የህወሓት መሪዎችን በሰላማዊ መንገድ ለጥያቄ ማቅረቡን ይጀምራል ያልነው የፀና እምነታችን በአመፃ መፈፀም መጀመሩ አስደንጋጭ ክስተት ሆኖብናል።
በዚህ ሳምንት መጨረሻ በመቐለ ከተማ በ4 የህወሓት ከፍተኛ ካድሬዎችና የጥቅም ተጋሪዎች፦ 1ኛ፤ ዶ/ር ፋና ሓጎስ (የትግራይ ክልል የፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንት) 2ኛ፤ ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ (የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ኣባል) 3ኛ፤ የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸው እንዳይጠቀስ ከፍተኛ የመረጃ አፈና ያካሄዱ አንድ የህወሓት አፈ-ቀላጤ 4ኛ፤ አንድ የህወሓት ባለስልጣናት የጥቅም ተጋሪ የሆኑ ልማታዊ ባለሃብት በድምሩ 4 የህወሓት ከፍተኛ ካድሬዎች ላይ ኣካላዊ ጥቃትና ዘረፋ መፈፀሙ ተረጋግጧል።
እኛም ህዝባችን በህወሓት መሪዎችና በስርዓቱ ላይ ፍፁም ተስፋ ቆርጦ ወደ ሃይል እርምጃ መግባት መጀመሩ የህዝባችን ጨዋነትና ሰላማዊነት ላይ መጥፎ ጥላ እንዳያጠላ ስጋት ገብቶናል።
ለዚህም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ጉዳዩን በከፍተኛ ትኩረት እንዲያጤኑትና በሰላማዊ መንገድ ስልጣን እስከማስረከብ የሚደረስ ሰላማዊ ድርድር ከወዲሁ እንዲጀመር በፅኑ እናሳስባለን።
Nebiyu Sihul Mikael


በዚህ ሳምንት መጨረሻ በመቐለ ከተማ በ4 የህወሓት ከፍተኛ ካድሬዎችና የጥቅም ተጋሪዎች፦ 1ኛ፤ ዶ/ር ፋና ሓጎስ (የትግራይ ክልል የፍርድ ቤቶች ፕሬዝዳንት) 2ኛ፤ ወ/ሮ ሰብለ ካሕሳይ (የህወሓት ማእከላይ ኮሚቴ ኣባል) 3ኛ፤ የጥቃቱ ሰለባ መሆናቸው እንዳይጠቀስ ከፍተኛ የመረጃ አፈና ያካሄዱ አንድ የህወሓት አፈ-ቀላጤ 4ኛ፤ አንድ የህወሓት ባለስልጣናት የጥቅም ተጋሪ የሆኑ ልማታዊ ባለሃብት በድምሩ 4 የህወሓት ከፍተኛ ካድሬዎች ላይ ኣካላዊ ጥቃትና ዘረፋ መፈፀሙ ተረጋግጧል።
እኛም ህዝባችን በህወሓት መሪዎችና በስርዓቱ ላይ ፍፁም ተስፋ ቆርጦ ወደ ሃይል እርምጃ መግባት መጀመሩ የህዝባችን ጨዋነትና ሰላማዊነት ላይ መጥፎ ጥላ እንዳያጠላ ስጋት ገብቶናል።
ለዚህም የሚመለከታቸው አካላት ሁሉ ጉዳዩን በከፍተኛ ትኩረት እንዲያጤኑትና በሰላማዊ መንገድ ስልጣን እስከማስረከብ የሚደረስ ሰላማዊ ድርድር ከወዲሁ እንዲጀመር በፅኑ እናሳስባለን።
Nebiyu Sihul Mikael

