ፍትሕ አልባዋና የወንጀለኞች መሸሸግያ መንደር!
Posted: 29 Mar 2020, 04:10
የትግራይ ፖሊስ ህግ ከማስከበር ይልቅ ህግ እየጣሰ የትግራይ ወጣት መግደል ቀጥሎበታል፣ የትግራይ ክልል ኮረና ቫይረስን ለመከላከል ባወጣው አዋጅ መሰረት፣ ወጣት ሓጎስ አዋጁን ለማስተግበር በሚንቀሳቀስበት ወቅት ስሙ ባልታወቀ ፖሊስ ዛሬ ተገድለዋል፣ የትግራይ የፀጥታ አካላት፣ አድዋ ከተማ ውስጥ በጠራራ ፃሃይ በቢላዋ እጅዋን እና አካላትዋን ጉዳት ያደረሰባት ወጣት በዋስ እንዲለቀቅ አድርገዋል፣ ዛሬም በወጣት ሓጎስ ላይ ግድያ የፈፀመ ፖሊስ ለህዝብ ይፋ ተደርጎ ፍርዱ በአፋጣኝ ማግኘት አለብት። የትግራይ ሙሁራን በትግራይ የሚፈፀም ግፍ መቃወም ሃጥያት ስለሚመላቸው ማንም ከነሱ ምንም አይጠብቅም፣ ትግራይ ውስጥ ፍትህ የሚነግስበት ጊዜ ቅርብ ነው፣ ለሟች ቤተሰብ መፅናናትን እየተመኘሁን የትግራይ ቲቪ ገዳዩ ለህዝብ ይፋ ታደርጉ ዘንድ እንጠይቃለን! ወንድማችን ሓጎስ ፈጣሪ ይቀበልህ። በትግራዋይ የሚገደል የትግራይ ወጣት; ትግራይ ውስጥ እያለ ፍትህ ለያየሰው የምትል ትግራዋይ አሁንም ልብ ግዛ!!



