ለመምከር ኮሚቴ አቋቋሙ
February 25, 2020 – Konjit Sitotaw — Comments ↓
FacebookTwitterEmailShare
ብልፅግና እና ህወሃት አብረው በሚሰሩበት ሁኔታ ላይ ለመምከር ኮሚቴ አቋቋሙ
የብልፅግና ፓርቲ መመስረትን ተከትሎ ከመስመሩ እራሱን ያገለለው ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ከአዲሱ ፓርቲ ጋር አብሮ መሄድ በሚያስችል ሁኔታ ላይ ለመምከር የጋራ ኮሚቴ መቋቋሙን የትግራይ ክልልን ከ 1987 ምርጫ አንስቶ እያስተዳደረ ያለው ድርጅት ሊቀ መንበር እና የክልሉ ምክትል ርእሰ መስተዳድር ደብረፂዮን ገብረሚካኤል (ፒኤች ዲ) በቅርቡ በመቐሌ ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ አስታወቁ፡፡
የክልሉር ምክትል ርእሰ መስተዳደር ከጋዜጠኞች ጋር በነበራቸው ቆይታ ስላሉ ችግሮች፣ ከኤርትራ ጋር ስላለው ግንኙነት፣ ስለለውጡ እና ስለ ተሸሸጉ ተጠርጣሪዎች ተናግረዋል፡፡