Page 1 of 1

በአዲስ አበባ የሰዎች ህይወት የጠፋበት የእምነት ቦታ ሌላ ‘ህጋዊ’ ባለቤት እና የመንግስት እጅ አለበት

Posted: 24 Feb 2020, 13:45
by Revelations
Please wait, video is loading...

Re: በአዲስ አበባ የሰዎች ህይወት የጠፋበት የእምነት ቦታ ሌላ ‘ህጋዊ’ ባለቤት እና የመንግስት እጅ አለበት

Posted: 24 Feb 2020, 14:09
by Revelations

Re: በአዲስ አበባ የሰዎች ህይወት የጠፋበት የእምነት ቦታ ሌላ ‘ህጋዊ’ ባለቤት እና የመንግስት እጅ አለበት

Posted: 24 Feb 2020, 14:31
by Revelations
የፓስተር ዮናታን ጉዳይ

የቦሌ ክፍለከተማው መሬት ህጋዊ ባለቤት ጉዳይ ባልተቋጨበት እንዲሁም ኦርቶዶክስ ቤተክርስቲያንም ጥያቄዋን አቅርባ ምላሽ ባላገኘችበት ሁኔታ የማርሲል ቲቪ ባለቤት ፓስተር ዮናታን አክሊሉ በቦታው ላይ የመልካም ወጣት ማእከል ለመገንባት ጥያቄ በዚህ አመት ታህሳስ ወር ላይ ጥያቄን ያቀርባል። ፓስተር ዮናታን ጥያቄውን ባቀረበ ወር በማይሞላ ጊዜ ውስጥ ቦታው እንደተፈቀደለት ዋዜማ ራዲዮ አረጋግጣለች።

ለፓስተር ዮናታን የመሬቱ ካርታ ጉዳይ እንዲያልቅለት የቦሌ ክፍለከተማ እና የአዲስ አበባ ከተማ መሬት አስተዳደር ደብዳቤ እንደተጻጻፉም ማወቅ ችለናል። ለፓስተር ዮናታን የመልካም ወጣት ማእከል ግንባታ ቦታው የተፈቀደበት መንገድ ብዙ ጥያቄ የሚያጭሩ ነገሮች ነበሩበት ። አንዱ ለ27 አመት ሲጓተት የነበረው የአንድ መሬት ጉዳይ ታህሳስ 2012 ዓ. ም በቀረበ ጥያቄ ወር በማይሞላ ጊዜ ምላሽ ማግኘቱ ብዙ ጥያቄ ያጭራል። እንዲሁም ለመልካም ወጣት ማእከል ቦታው ይሰጥ እስኪባል ድረስ መሬቱ ለአረንጓዴ ልማት ይሁን ተብሎ ከአመታት በፊት በተወሰነው ውሳኔ የተቀመጠ ነው ( ምንም እንኳ ይህም ውሳኔ ህገወጥ ቢሆንም) ።

የፓስተር ዮናታን ጥያቄን ተከትሎ ታድያ ቦታው ከአረንጓዴ ልማትነት ወደ ቅይጥ አገልግሎት እንዲቀየር ተደረገ። ይህ እጅግ ሊመረመር እና ተጠያቂነትን ማስከተል ያለበት ውስብስብ ጉዳይ ሆኖ አግኝተነዋል። ነገሩ በካቢኒ አለመወሰኑን ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማም ነገሩን እንደማያውቁት መገለጹ ይታወሳል። ለመልካም ወጣት ማእከል ግንባታ ቦታው መፈቀዱ ውስጥ ለውስጥ ሲሰማ ታድያ የኦሮቶዶክስ ቤተክርስቲያን ቦታው ላይ ቤተክርስቲያን በመስራት ለምእመናን አገልግሎት መስጠት ትጀምራለች። የዚህም መነሻ ለበርካታ አመታት ጥያቄ ቀርቦ ሳለ ለቅርብ ጥያቄ ፈጣን ምላሽ ለምን ተሰጠ በሚል ነው።

በይዞታው ላይ ይህ ሁሉ እንቅስቃሴ ሲደረግ የመሬቱ ህጋዊ ባለቤት አቶ ሪያድ በቦታው ላይ ያለውን እንቅቃሴ በፍርድ ቤት ሊጠይቁ እንቅስቃሴ ላይ ነበሩ።በዚህ መሀል ከጥቂት ሳምንታት በፊት በሌሊት ህግ እናስከብራለን ባሉ የጸጥታ አካላት በተተኮሰ ጥይት ሁለት ወጣቶች ህይወታቸው አልፏል፣ በርካቶችም ቆስለዋል።

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን አሁን ወጣቶች የተገደሉበት ቦታ ቤተክርስቲያን እንዲሰራበት በቅዱስ ሲኖዶስ በኩል ጥያቄን አቅርባለች። ዋዜማ ራዲዮ ግን መሬቱ ህጋዊ ባለቤት ናቸው ለተባሉት አቶ ሪያድ ደማጅ እንዲሰጥ የመጨረሻ ውሳኔ እየተጠበቀ መሆኑን ሰምታለች። [ዋዜማ ራዲዮ]

Re: በአዲስ አበባ የሰዎች ህይወት የጠፋበት የእምነት ቦታ ሌላ ‘ህጋዊ’ ባለቤት እና የመንግስት እጅ አለበት

Posted: 24 Feb 2020, 14:52
by Revelations

Re: በአዲስ አበባ የሰዎች ህይወት የጠፋበት የእምነት ቦታ ሌላ ‘ህጋዊ’ ባለቤት እና የመንግስት እጅ አለበት

Posted: 24 Feb 2020, 22:40
by Revelations