Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Hameddibewoyane
Member
Posts: 3890
Joined: 25 Sep 2019, 02:42

ለውጥ አይቀሬ ነው!

Post by Hameddibewoyane » 16 Feb 2020, 02:58

ይህ ግፍ በትግራይ እየተፈፀመ ዝምታ የመረጣቹ የትግራይ ሙሁራን ነገ በናንተም ይደርሳል፣ ትግራይ ለሁሉም ትግራዋይ እኩል እስከምት ሆን ድረስ ትግላችን ይቀጥላል፣ ለካቲት ፩፩ የሚከበረው ህወሓት በትግራይ ለዛውም በተጋሩ ጭፍጨፋ እያካሄደች ባለችበት ወር ነው።

ትናንት በብሄራቸው ብቻ ነው የታሰሩት ያላቹህን የቀድሞ የህወሓት ባለስልጣናት መታሰር ትክክል ነው የምንለው፣ ህወሓት በትግራይ በፖለቲካ አመለካከታቸው ብቻ የምታስራቸው ተጋሩ ስላለ ነው፣ የዚህ መጨረሻ በትግራይ የትግራይ መሳፍንት ታሪክ ተደግሞ፣ ህወሓት ላንዴ እና ለመጨረሻ የምትጠፋበት ጊዜ ቅርብ ነው፣ ያኔ ሂሳብ ማወራረዱም ይቀጥላል። ዝምታ የመረጥከው የትግራይ ሙሁር፣ ህወሓት በአደባባይ ትግራይ ውስጥ የትግራይ ወጣቶች ከተማ ውስጥ መረሸን ስትጀምር የሚገባህ ከሆነ ጊዜ ለኩሉ። ዶ/ር ማርቆስ አይዞህ ይህም ያልፋል።