ስሟ እንዳይጠቀስ የጠየቀችና በኤርትራ ወታደር የነበረች ስደተኛ ከጓደኛዋ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጣ ከገባች ስድስት ቀን እንደሆናት ተናግራለች። ግን አንመዘግብም አሉን ትላለች
Posted: 13 Feb 2020, 10:14
‘’ ቦታውን በግልጽ አላወቃችሁትም፤ሁለታችሁ የምትናገሩት ሠዓት የተለያየ ነው። ስለዚህ አንመዘግብም' አሉን"
………………………………………………………………………………….............
ኤርትራውያን ከሀገራቸው ወጥተው ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ በድንበር አካባቢ ምዝገባ እንደሚደረግ ይታወቃል። ከዚያ በኋላም ወደ ምዕራብ ትግራይ እንዳ'ባጉና ከተማ ይመጡ ነበር።
እዚህ ስፍራም ስለግለሰቦቹ አስፈላጊው መረጃ ከተጠናቀረ በኋላ ወደ ስደተኞች መጠለያ እንዲገቡ የሚደረግበት አካሄድ ነበር።
ዛላንበሳ ድንበር ፋፂ ከተማ እስካሁን ኤርትራውያን ስደተኞችን እየመዘገቡ ሲያስገቡ የነበሩ የፌደራል መንግሥት የስደተኞችና የስደት ተመላሾች ተቋም ሠራተኞች 'አንመዘግብም' ማለታቸውን ቢቢሲ ከስደተኞቹ መረዳት ችሏል።
ስሟ እንዳይጠቀስ የጠየቀችና በኤርትራ ወታደር የነበረች ስደተኛ ከጓደኛዋ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጣ ከገባች ስድስት ቀን እንደሆናት ለቢቢሲ ተናግራለች።
ነገር ግን ፋፂ አካባቢ የሚገኙ ስደተኞችን የሚመዘግቡ አካላት ግን ሊመዘግቧቸው ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ታስረዳለች "ወታደሮች እንደነበርንና ለድንበር አሻጋሪ ደላሎች 40 ሺህ ናቅፋ ከፍለን እንደመጣን ነገርናቸው። 'የመጣችሁበትን ቦታ ግልጽ ተናገሩ' አሉን። ምን ያህል ቀን እንደተጓዝን እና ሠንዓፈ ከተማ እንደደረስን አስረዳን። ' ቦታውን በግልጽ አላወቃችሁትም። ሁለታችሁ የምትናገሩት ሠዓት የተለያየ ነው። ስለዚህ አንመዘግብም' አሉን" ብላለች።
ቢቢሲ ከተቋሙ መደበኛ ባልሆነ መልኩ ባገኘው መረጃ መሰረት ከሆነ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ኤርትራውያን ስደተኞችን የመመዝገቢያ አዲስ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል።
ይሁን እንጂ ይህ አሰራር በይፋ ለተገልጋዮች አልተገለጸም።
https://bbc.in/2USXGz9
………………………………………………………………………………….............
ኤርትራውያን ከሀገራቸው ወጥተው ወደ ኢትዮጵያ ሲገቡ በድንበር አካባቢ ምዝገባ እንደሚደረግ ይታወቃል። ከዚያ በኋላም ወደ ምዕራብ ትግራይ እንዳ'ባጉና ከተማ ይመጡ ነበር።
እዚህ ስፍራም ስለግለሰቦቹ አስፈላጊው መረጃ ከተጠናቀረ በኋላ ወደ ስደተኞች መጠለያ እንዲገቡ የሚደረግበት አካሄድ ነበር።
ዛላንበሳ ድንበር ፋፂ ከተማ እስካሁን ኤርትራውያን ስደተኞችን እየመዘገቡ ሲያስገቡ የነበሩ የፌደራል መንግሥት የስደተኞችና የስደት ተመላሾች ተቋም ሠራተኞች 'አንመዘግብም' ማለታቸውን ቢቢሲ ከስደተኞቹ መረዳት ችሏል።
ስሟ እንዳይጠቀስ የጠየቀችና በኤርትራ ወታደር የነበረች ስደተኛ ከጓደኛዋ ጋር በመሆን የኢትዮጵያን ድንበር አቋርጣ ከገባች ስድስት ቀን እንደሆናት ለቢቢሲ ተናግራለች።
ነገር ግን ፋፂ አካባቢ የሚገኙ ስደተኞችን የሚመዘግቡ አካላት ግን ሊመዘግቧቸው ፈቃደኛ አለመሆናቸውን ታስረዳለች "ወታደሮች እንደነበርንና ለድንበር አሻጋሪ ደላሎች 40 ሺህ ናቅፋ ከፍለን እንደመጣን ነገርናቸው። 'የመጣችሁበትን ቦታ ግልጽ ተናገሩ' አሉን። ምን ያህል ቀን እንደተጓዝን እና ሠንዓፈ ከተማ እንደደረስን አስረዳን። ' ቦታውን በግልጽ አላወቃችሁትም። ሁለታችሁ የምትናገሩት ሠዓት የተለያየ ነው። ስለዚህ አንመዘግብም' አሉን" ብላለች።
ቢቢሲ ከተቋሙ መደበኛ ባልሆነ መልኩ ባገኘው መረጃ መሰረት ከሆነ ከቅርብ ጊዜ ጀምሮ ኤርትራውያን ስደተኞችን የመመዝገቢያ አዲስ አሰራር ተግባራዊ ማድረግ ጀምሯል።
ይሁን እንጂ ይህ አሰራር በይፋ ለተገልጋዮች አልተገለጸም።
https://bbc.in/2USXGz9