ለጃዋር መሐመድ መንግስት የመደባቸው ጥበቃዎች መነሳታቸው ተሰማ
Posted: 06 Feb 2020, 17:34
በቅርቡ ኦፌኮን የተቀላቀሉት ጃዋር መሃመድ የፌደራል ፖሊስ ሲያደርግላቸው የነበረውን ጥበቃ ከ እሁድ ጥር 17/2012 ጀምሮ ማንሳቱን የኦሮሚያ ብሮድካስት ኮርፖሬሽን አስታወቀ፡፡
ኦቢኤን በምሽት ሁለት ሰአት ዜናው ላይ አንዳስነበበው መንግስት ለማንኛውም ተፎካካሪ ፓርቲ አመራርም ሆነ አባል የግል ጥበቃ ስለማያደርግ እና አሰራሩም ስለማይፈቅድ ጥበቃዎቹ እንደተነሱ ፌደረላ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
አዲስ ማለዳም ባደረገችው ማጣራት ጃዋር ጠባቂዎቻቸው ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርጉ የፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዘርፍ በፃፈው ደብዳቤ ማስታወቁን አረጋግጣለች፡፡
አዲስ ማለዳ ወደ ጃዋር መሃመድ በተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ብታደርግም ለግዜው አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
https://mereja.com/amharic/v2/215003
ኦቢኤን በምሽት ሁለት ሰአት ዜናው ላይ አንዳስነበበው መንግስት ለማንኛውም ተፎካካሪ ፓርቲ አመራርም ሆነ አባል የግል ጥበቃ ስለማያደርግ እና አሰራሩም ስለማይፈቅድ ጥበቃዎቹ እንደተነሱ ፌደረላ ፖሊስ አስታውቋል፡፡
አዲስ ማለዳም ባደረገችው ማጣራት ጃዋር ጠባቂዎቻቸው ወደ መደበኛ ስራቸው እንዲመለሱ እንዲያደርጉ የፌደራል ፖሊስ የወንጀል መከላከል ዘርፍ በፃፈው ደብዳቤ ማስታወቁን አረጋግጣለች፡፡
አዲስ ማለዳ ወደ ጃዋር መሃመድ በተደጋጋሚ የስልክ ጥሪ ብታደርግም ለግዜው አስተያየት ከመስጠት ተቆጥበዋል፡፡
https://mereja.com/amharic/v2/215003