የቴፒ ህዝብ እየተሰደደ ነው:: #Inbox የተላኩልኝ ፎቶዎች እጅግ አሰቃቂ ስለሆኑ ፖስት ማድረግ አልፈለኩም ::
#Ethiopia : ሰላም ናቲ ከዚህ በፊት አንዴ መረጃ ልኬልህ ነበር.. ,ቴፒ በ27 አመቱ የወያኔ የዘር ፖለቲካ አሳሯን ስትበላ የከረመች በደቡብ ምእራብ የምትገኝ በብዙ ብሄር የታጀበች ትንሽ ከተማ ነች ። የምትገኝበት ዞን ሸካ ሲሆን የዞን መዋቅር ስልጣኑን ጠቅልለው ያያዙት የሸካ ብሄር በመሆናቸው እና የአከባቢው ተወላጅ የሚደርስበትን ብሄር ተኮር ጥቃትና የፖለቲካ ገለልተኝነት እንዲሁም የመልካም አስተዳደር በደሎች ተደራርበው በተለያዩ ግዜያት ግጭቶች ተነስተው የበርካታ ንፁሃን ዜጎችን ህይወት አሳጥቷል። ይህ በእንዲህ እንዳለ ከዶ/ር አብይ የለውጥ አመራር ጋር ተያይዞ የቴፒ ህዝብ የነፃነት አየር ለመተንፈስ ቢቋምጥም ሁሉም ነገር ከመሻሻል ይልቅ ከድጡ ወደማጡ ሆኖ ይኸው ላለፉት 1 አመት ከ8 ወራት ያክል በኮማንድ ፖስት ስር ሆና ከ150 በላይ ንፁሃን ዜጎቿን ሰዉታለች።
እኔም በቅርቡ ታላቅ ወንድሜን ኢ-ሰብአዊ በሆነ መልኩ(በ 5 ጥይት )ተደብድቦ ተገሎብኛል።
የመንግስት ያለህ ብንልም የሚሰማን አጣን።
ናቲ ኢትዮጵያን እንደምትወዳት አውቃለሁ በኢትዮጵያ አምላክ ይዤሀለው ቴፒን መንግስት እንዲደርስላት አድርግ። የቀድሞ የህወሃት ተላላኪዎች ቴፒን አኬልዳማ እያደረጓት ነውና እባክህን የኢትዮጵያዊነት ግዴታህን ተወጣ !
እኔ የምፈልገው ትላንት በደቡብ ክልል ልዩ ሀይል በጅምላ ስለተገደሉት 20 ሰዎች እና ስለቆሰሉት 16 ሰዎች ፖስት እንድታደርግልኝ ብቻ ሳይሆን መንግስት የቴፒን ስር ነቀል ችግር በዘላቂነት እንዲፈታም ጭምር ግፊት እንድታደርግልኝ ነው።
ናቲ አቅም እንዳለህ አውቃለሁ ! ሰዎችን ታገኛለህ አመሰግናለሁ ናቲ.... ምንም አይነት መረጃ ከፈለክ ፃፍልኝ በነገራችን ላይ ብዙ የቴፒ ከተማና የአከባቢው ወጣቶች የመንግስትን ችላ ባይነት ተመልክተው ጫካ ገብተዋል። ምንም እንኳን በዚህን ሰአት ነፍጥ ይዞ ጫካ መግባቱ የሚደገፍ የፖለቲካ አካሄድ ባይሆንም በልዩ ሀይል ጥይት ቤት ሆኖ ከመሞት ጫካ መግባቱን መርጠዋል።

