Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Ejersa
Member
Posts: 3978
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

ሰበር ዜና:- በወለጋ ተማሪዎቹን "ያገቷቸው" ተማሪዎች ናቸው! ታጋቾቹ 26 ሲሆኑ 21 ተለቀው 5 ይቀራሉ!

Post by Ejersa » 12 Jan 2020, 15:14

ጀመሪያ 17 ተማሪዎች ታገቱ ተባለ። ትላንት ደግሞ የጠቅላይ ሚኒስትር ፅ/ቤት ሃላፊው አቶ ንጉሡ ጥላሁን 21 ተማሪዎች ተለቀዋል ማለታቸው ይታወሳል። በዚህ መሠረት መታገታቸው ያልተሰማ 4 ተማሪዎች አሉ ማለት ነው። BBC አማርኛ ደግሞ ተማሪዎቹን ቤተሰቦች አናግሮ "በሚዲያ ተለቅቀዋል" መባሉን ከመስማታቸው በስተቀር የሚያውቁት ነገር እንደሌለ ዘግቧል። የደምቢዶሎ ዩኒቨርስቲም ተመሣሣይ አስተያየት መስጠቱ ተሰምቷል። ስለዚህ ማንን እንመን? ስለታገቱት ተማሪዎች ትክክለኛው መረጃ የቱ ነው? እትጌ Meskerem Abera እነዚህንና ሌሎች ጥያቄዎችን እያነሳች ስለወተወተችኝ ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉ ከፍተኛ የመንግስት ሃላፊ ጋር ስልክ ደወልኩና ጉዳዩን አጣራሁ። ነገሩ እንደዚህ ነው፤

በመጀመሪያ ደረጃ ከ16 ዩኒቨርስቲዎች ወጥተው ወደ ቤተሰቦቻቸው የሄዱ 35ሺህ ተማሪዎች አሉ። ኸእነዚህ ውስጥ ግማሹ ቤተሰቦቹ ጋር ደርሷል፤ ሌላው መንገድ ላይ ይሆናል፣ ከፊሉ ወደ ቤቱ ሳይሄድ ከተማ ውስጥ አንዱ ጋር ተቀምጧል፤ ጥቂቶች ደግሞ ጫካ ውስጥ አድፍጠው ተማሪዎች #ያግታሉ። ተሳስቼ አይደለም‼ አዎ... ከደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ወጥተው ወደ ቤተሰቦቻቸው በመሄድ ላይ የነበሩ ተማሪዎችን መጀመሪያ ላይ ያገቷቸው የኦነግ ሸኔ ታጣቂዎች ወይም ጃል ማሮ አይደለም። ከዚያ ይልቅ በአማራ ክልል በሚገኙ ዩኒቨርስቲዎች ይማሩ የነበሩና ሰሞኑን በተፈጠረው ችግር ምክንያት ወደ ትውልድ ስፍራቸው የተመለሱ የደምቢዶሎ አከባቢ ተወላጅ የሆኑ የዩኑቨርሲቲ ተማሪዎች ናቸው።ሆኖም ግን "ተማሪዎቹን ያገተው ኦነግ ሸኔ ነው" እየተባለ በሰፊው ስለተወራ ጃል ማሮ ራሱ አጋቾቹ ያሉበትን ቦታ አፈላልጎ ማግኘቱና አስፈላጊውን ድጋፍና ጥበቃ ማድረጉ አይቀርም። ምክንያቱም፤ አንደኛ፦ ነገሩ ከፍተኛ የሆነ ፕሮፓጋንዳ እየተሰራበት ነው፣ ሁለተኛ፦ ድርጊቱ የተፈፀመው በስሙ ነው፣ ሦስተኛ፦ መንግሥት ከሚወስደው እርምጃ በተጨማሪ በማህብረሰብ ደረጃ የሚያስከትለው ጣጣ ብዙ ነው። ስለዚህ አክቲቪስት የተባለ ሁሉ "ኦነግሸኔ የአማራ ተማሪዎችን አገተ!" እያለ ወሬውን ሲያራግብ ልጆቹን ከአጋቾቹ ተማሪዎች አሳልፎ ለጃል ማሮ ታጣቂዎች ሰጣቸው። "ጉድ በል ጎንደር!" ማለት ይሄኔ ነው።

በመጨረሻም ጎረምሶቹ ያገቷቸው ተማሪዎች ብዛት 27 ነበር። ከእነዚህ ውስጥ አንዷ በራሷ አምልጣ ቤተሰቦቿ ጋር ሄዳለች። እዚህ ጋር ልጅቷ ከBBC ጋር ባደረገችው ቃለምልልስ "ወጠምሻዎቹ ከሌሎች ተማሪዎች ጋር በዚህ ሂዱ እያሉ ሲጨቃጨቁ ቀስ ብላ እንዳመለጠች ተናግራለች። ማይ ፍሬንድ ክላሽ የታጠቀ አጋች ሂድ አትሂድ እያለ አይጨቃጨቅም። አንተም ከአጋቾቹ ጋር አትሳፈጥም። ይህቺ ልጅ ግን "...ካመለጥኩ በኋላ ጫካ ውስጥ ሁለት ቀን አድሬ አንድ አባት አገኙኝ። እሳቸውም የእኔስ ልጆች ቢሆኑ እንዲህ አይደል የሚሆኑት ብለው ኮታቸውን አለቀሱኝ። ከዛ ሸኙኝ..." ጲሪሪሪሪ ወራጅ አለ‼ ከልጅቷ አነጋገር ሁለት ቀን ጫካ ውስጥ ያደረች አይመስልም። ከዚያ ይልቅ መረጃውን እንድታወጣ የለቀቋት ይመስላል። ለመሆኑ BBC አማርኛ የልጅቷን እና የተማሪዎቹን ቤተሰቦች ስልክ መቼና እንዴት አገኘ? ኦኦ... ስልክ ስል ትዝ... አለኝ። ልጅቷ ከታገቱት ልጆች ጋር በስልክ ታወራ እንደነበር ገልፃ ስልኩም የአጋቾቹ እንደሆነ ለBBC ተናግራለች። የራሱን ስልክ ሰጥቶ ያለበትን ቦታ ለደህንነት ሰዎች የሚናገር አጋች!! ሆሆይ... ለማንኛውም ከቀሩት 26 ተማሪዎች ውስጥ ትላንት 21ዱ ተለቅቀዋል። በዚህ መሠረት አሁን 5 ተማሪዎች ይቀራሉ። የጠቀስኩት የመንግስት ሃላፊ እንደነገረኝ የቀሩትን ተማሪዎች ለማስለቀቅ በሰከነ መልኩ እየተሰራ ነው። ነገሩን ያለ ቅጥ ማራገብ የባሰ ችግሩን ከማወሳሰብ የዘለለ ፋይዳ የለውም። ይህን ጉዳይ በማቀነባበር ረገድ ተሳታፊ የሆኑት አካላት፦ የኦነግ ሽኔ ደጋፊዎች፣ የአማራ ሸኔ ብሔርተኞች፣ የBBC አማርኛ ባልደረቦች፣ የበጀትና ሎጅስቲክ ድጋፍ እነ አንቶኒዎች። BBC አማርኛ ሲከፈት ጃዋር ኬኒያ ድረስ ሄዶ የሰጣቸው መመሪያ ምን እንደሆነ አሁን በደንብ እየገባኝ ነው።

Maxi
Member+
Posts: 5951
Joined: 06 Mar 2014, 04:33

Re: ሰበር ዜና:- በወለጋ ተማሪዎቹን "ያገቷቸው" ተማሪዎች ናቸው! ታጋቾቹ 26 ሲሆኑ 21 ተለቀው 5 ይቀራሉ!

Post by Maxi » 12 Jan 2020, 15:20

ቀዳዳ ነህ!! ይህን የአማራ ብዙሃን ዛሬ ከአንድ ሰዓት በፊት የዘገበው ዜና አንብበው እስኪ!!




Amhara Mass Media Agency

‹‹ተለቀቁ ሲባል በመገናኛ ብዙኃን ከመስማታችን የተለዬ ነገር አልሰማንም፡፡›› የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ወላጆች

በታጋቾች ቁጥጥር ሥር ከነበሩ የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል 21 ትናንት መለቀቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

አብመድ ዛሬ ወደ ታጋች ቤተሰቦች ደውሎ ከልጆቻቸው ጋር በስልክ መገናኘት ስለመቻል አለመቻላቸው ጠይቋል፡፡ የተለቀቁም ያልተለቀቁም ተማሪዎች እንዳሉ በመገናኛ ብዙኃን ከመስማታቸው ውጭ አዲስ ተጨባጭ መረጃ እንዳላገኙ ነው ቤተሰቦች የተናገሩት፡፡ ‹‹መግለጫውን በመገናኛ ብዙኃን ከመስማት ውጭ የሰማነው ነገር የለም፤ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ ሲደውሉልን የነበረም በአጋቾች ስልክ ነው፤ ያም ስልክ አይሠራም፤ የልጃችንም ስልክ አይሠራም፡፡ አጋቾች ሲያገናኙንም ልጆቹ ‹‹ደህና ነን› ከማለት በቀር ሌላ መረጃ አልሰጡንም ነበር›› ብለዋል የአንደኛዋ ታጋች ተማሪ ቤተሰብ፡፡

ሌላኛው የታጋች ተማሪ አባት ደግሞ ‹‹እኔ ተለቀቁ ሲባል ስሰማ በጣም ተደስቼ ነበር፤ ግን ይኸው እስከ ዛሬ 6፡00 ድረስ የልጄን ድምጽ አልሠማሁም፡፡ መቼም ልጄ ምን ያህል እንደምንጨነቅ አታጣውም፤ ከተለቀቁ እንዴት የሌላ ሰው ስልክ ለምና እንኳን አትደውልልንም? መንግሥትስ የተለቀቁትን ተማሪዎች ዝርዝር ለምን አይነግረንምና ቁርጣችን አናውቅም?›› ብለዋል፡፡

ሌላኛው የታጋች ቤተሰብም ተመሳሳይ አስተያዬት ነው የሰጡን፤ ‹‹መግለጫውን እንደሰማን በጉጉት መጠበቅ ጀምረን ነበር፤ ግን ይኸው መሽቶ ነጋ፤ አዲስ የሰማነው ነገር የለም፡፡ የልጃችንን ድምጽም አልሰማንም›› ብለዋል፡፡

ልጆቹ ከታገቱ በኋላ በአጋቾች ስልክ ሁለት ጊዜ አገናኝተዋቸው እንደነበረ ያስታወሱት የታጋች ቤተሰብ ‹‹ሌሊት ሌሊት ስለሚያጓጉዙን የት እንዳለን አናውቅም፤ ብቻ ደኅና ነን፤ ምግብም ያቀርቡልናል›› እንዳለቻቸው አስታውሰዋል፡፡ በቅርብ ሳምንታትም ደውላ እንደማታውቅም ተናግረዋል፡፡ ‹‹ተማሪዎች እንደሚባለው ተለቅቀው ከሆነ ስለምን ስልክ ወደ ቤተሰብ እንዲደውሉ አይደረግም? ወደ ቤተሰቦቻቸውስ ለምን አይልኳቸውም?›› ሲሉም ጠይቀዋል፡፡

አብመድ ተለቀቁ ስተባሉት ተማሪዎች ዝርዝር መረጃ ለማግኘት በደምቢዶሎ አካባቢ ከሚገኙ የፀጥታ አካላት፣ ከፌዴራል መንግሥትና ከኦሮሚያ ክልል መንግሥት መረጃ ለማግኘት ጥረት እያደረገ ነው፤ እስካሁን መረጃ ማግኘት አልቻለም፤ እንዳገኘ የሚያደርስ ይሆናል፡፡

ዘጋቢ፡- አብርሃም በዕውቀት

Please wait, video is loading...

Ejersa
Member
Posts: 3978
Joined: 05 Nov 2019, 10:39

Re: ሰበር ዜና:- በወለጋ ተማሪዎቹን "ያገቷቸው" ተማሪዎች ናቸው! ታጋቾቹ 26 ሲሆኑ 21 ተለቀው 5 ይቀራሉ!

Post by Ejersa » 12 Jan 2020, 15:28

Be cool! The idiot Neftegna, you will certify the reality the sooner possible from different sources. An insult is the justification for your capacity & knowledge
quote=Maxi post_id=1000845 time=1578856810 user_id=42531]
ቀዳዳ ነህ!! ይህን የአማራ ብዙሃን ዛሬ ከአንድ ሰዓት በፊት የዘገበው ዜና አንብበው እስኪ!![/size]




Amhara Mass Media Agency

‹‹ተለቀቁ ሲባል በመገናኛ ብዙኃን ከመስማታችን የተለዬ ነገር አልሰማንም፡፡›› የደንቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ታጋች ተማሪዎች ወላጆች

በታጋቾች ቁጥጥር ሥር ከነበሩ የደምቢዶሎ ዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች መካከል 21 ትናንት መለቀቃቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽሕፈት ቤት ማስታወቁ ይታወሳል፡፡

አብመድ ዛሬ ወደ ታጋች ቤተሰቦች ደውሎ ከልጆቻቸው ጋር በስልክ መገናኘት ስለመቻል አለመቻላቸው ጠይቋል፡፡ የተለቀቁም ያልተለቀቁም ተማሪዎች እንዳሉ በመገናኛ ብዙኃን ከመስማታቸው ውጭ አዲስ ተጨባጭ መረጃ እንዳላገኙ ነው ቤተሰቦች የተናገሩት፡፡ ‹‹መግለጫውን በመገናኛ ብዙኃን ከመስማት ውጭ የሰማነው ነገር የለም፤ ቀደም ብሎ አልፎ አልፎ ሲደውሉልን የነበረም በአጋቾች ስልክ ነው፤ ያም ስልክ አይሠራም፤ የልጃችንም ስልክ አይሠራም፡፡ አጋቾች ሲያገናኙንም ልጆቹ ‹‹ደህና ነን› ከማለት በቀር ሌላ መረጃ አልሰጡንም ነበር›› ብለዋል የአንደኛዋ ታጋች ተማሪ ቤተሰብ፡፡

ሌላኛው የታጋች ተማሪ አባት ደግሞ ‹‹እኔ ተለቀቁ ሲባል ስሰማ በጣም ተደስቼ ነበር፤ ግን ይኸው እስከ ዛሬ 6፡00 ድረስ የልጄን ድምጽ አልሠማሁም፡፡ መቼም ልጄ ምን ያህል እንደምንጨነቅ አታጣውም፤ ከተለቀቁ እንዴት የሌላ ሰው ስልክ ለምና እንኳን አትደውልልንም? መንግሥትስ የተለቀቁትን ተማሪዎች ዝርዝር ለምን አይነግረንምና ቁርጣችን አናውቅም?›› ብለዋል፡፡

ሌላኛው የታጋች ቤተሰብም ተመሳሳይ አስተያዬት ነው የሰጡን፤ ‹‹መግለጫውን እንደሰማን በጉጉት መጠበቅ ጀምረን ነበር፤ ግን ይኸው መሽቶ ነጋ፤ አዲስ የሰማነው ነገር የለም፡፡ የልጃችንን ድምጽም አልሰማንም›› ብለዋል፡፡

ልጆቹ ከታገቱ በኋላ በአጋቾች ስልክ ሁለት ጊዜ አገናኝተዋቸው እንደነበረ ያስታወሱት የታጋች ቤተሰብ ‹‹ሌሊት ሌሊት ስለሚያጓጉዙን የት እንዳለን አናውቅም፤ ብቻ ደኅና ነን፤ ምግብም ያቀርቡልናል›› እንዳለቻቸው አስታውሰዋል፡፡ በቅርብ ሳምንታትም ደውላ እንደማታውቅም ተናግረዋል፡፡ ‹‹ተማሪዎች እንደሚባለው ተለቅቀው ከሆነ ስለምን ስልክ ወደ ቤተሰብ እንዲደውሉ አይደረግም? ወደ ቤተሰቦቻቸውስ ለምን አይልኳቸውም?›› ሲሉም ጠይቀዋል፡፡

አብመድ ተለቀቁ ስተባሉት ተማሪዎች ዝርዝር መረጃ ለማግኘት በደምቢዶሎ አካባቢ ከሚገኙ የፀጥታ አካላት፣ ከፌዴራል መንግሥትና ከኦሮሚያ ክልል መንግሥት መረጃ ለማግኘት ጥረት እያደረገ ነው፤ እስካሁን መረጃ ማግኘት አልቻለም፤ እንዳገኘ የሚያደርስ ይሆናል፡፡

ዘጋቢ፡- አብርሃም በዕውቀት

Please wait, video is loading...
[/quote]

Post Reply