የትግራይ ህዝብ ኋላቀር በሆነ መንገድ ለህዉሃት ፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ መሆን የለበትም- አቦ ተስፋዬ ገብረአብ
Posted: 05 Jan 2020, 17:15
የትግራይ ህዝብ ኋላቀር በሆነ መንገድ ለህዉሃት ፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ መሆን የለበትም
~~~~~~~~~~
አምባገነኑ የህዉሃት ስርዓት ከተጠነሰሰ ጀምሮ ከሴራ ፖለቲካ ተላቆ አያዉቅም፡፡ ዘመኑን ያሳለፈዉ በተንኮል፣ በሴራና በጥፋት እንጂ መልካም ነገርን በመፈጸም አይድለም፡፡ ለመልካም ነገር ያልታደሉት የህዉሃት አንጋፋ ካድሪዎች የትግራይን ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጲያዊያን ጋር ለመነጠልና በጥርጣሬ እንዲተያይ የሚያደርጉትን ሴራ የትግራይ ህዝብ በዝምታ ማለፍ የለበትም፡፡
የትግራይ ህዝብ በተራ የህዉሃት ካድሪዎች ፕሮፖጋንዳ ከኢትዮጲያዊነቱ እንዲሸሽ የሚደረገዉን ሴራ በጥንቃቄ መረዳት አለበት፡፡ የትግራይ ህዝብ ጽኑ ፍላጎት ልማት፣ዴሞክራሲና ሰላም እንጂ ልዩነትና ጥላቻ አይድለም፡፡ ከህዉሃት የተለመደ የዉሸት ፕሮፖጋንዳ ያተረፈዉ ጥላቻና መከፋፈልን ነው፡፡
እድሜ ዘመናቸዉን የኢትዮጲያን ህዝብ ባይተዋር አድርገዉ የሃገርና የህዝብ ሃብት በመዝርፍ የናጠጠ ኑሮ የሚኖሩ የህዉሃት ካድሪዎች ዛሬም የትግራይን ህዝብ ከእኛ በላይ ላሳር በሚል አስተሳሰብ በተናጠል ሊሸነግሉት አይገባም፡፡
ላለፉት 30 እና 40 ዓመታት ወንበር ላይ ቁጭ ብለዉ የኖሩ የስርዓቱ ተላላኪ የነበሩ ግለሰቦችን ካሉበት እያፈላለጉ የትግራይን ህዝብ የድሮ ስርዓት ተመለሰ በሚል ከሌሎች ህዝቦች ጋር በጥርጣሬ እንዲተያይ አድርገዉ የስልጣን ዘመናቸዉን ማራዘም ይፈልጋሉ፡፡
በህዉሃት የስልጣን ዘመን ፍጹም ተግባራዊ ሲደረግ ያልነበረን የዉሸት ህገ መንግስትና የፌድራል ስርዓት ዛሬ ህገ መንግስቱ ተናደ፣ የፌድራል ስርዓቱ ፈረሰ በሚል አጉል መፈክር የትግራይን ህዝብ የፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ ማድረግ ተገቢነት የለዉም፡፡
የይስሙላ ፌድራሊዝም ስርዓት ዘርግቶ የኢትዮጲያን ህዝብ ከፋፍሎ እንደሉቡ ሲያደርግ የኖረዉ አምባገነን የህዉሃት ካድሪዎች ቡድን በኢትዮጲያ ህዝብ ለዉጥ ፈላጊነት ምክኒያት ተገፍተዉ መቀለ ከመሸገ በኋላም በዘረፈዉ ገንዘብ ሃገርንና ህዝብን ከማተራመስ አልታቀበም፡፡
ዛሬም በህዉሃት የሴራ ማንፌስቶ አስተሳሰብ የተቀረጹና በለዉጡ ምክኒያት ከስልጣን የተገለሉ ነባር የአማራና የኦሮሞ ሰዎችን ይዘዉ የፌድራሊዝምና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ተጣሰ ሲሉ ይደመጣል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሰዎች ህገ-መንግስቱም ይሁን የፌድራል ስርዓቱን እንኳን ሊያከብሩት ቀርቶ መኖሩን እንኳ አስበዉት አያዉቁም፡፡ እንዲህ ብለዉ ወመያየታቸዉ በራሱ ኢሉኝታ ማጣት ነዉ፡፡
በስልጣን ዘመናቸዉ ህገ መንግስቱ ቢከበር ኖሮ በርካታ ኢትዮጲያዊያን ቶርች አይደረጉም ነበር፡፡ ለአሰቃቂ ስርና እንግልት አይዳረጉም ነበር፡፡ የመብት አፈናም አይፈጸምባቸዉም ነበር፡፡ የነበረዉ ስርዓት ለባለጊዜዎች የተመቸ የይስሙላ ስርዓት ነው፡፡
~~~~~~~~~~
አምባገነኑ የህዉሃት ስርዓት ከተጠነሰሰ ጀምሮ ከሴራ ፖለቲካ ተላቆ አያዉቅም፡፡ ዘመኑን ያሳለፈዉ በተንኮል፣ በሴራና በጥፋት እንጂ መልካም ነገርን በመፈጸም አይድለም፡፡ ለመልካም ነገር ያልታደሉት የህዉሃት አንጋፋ ካድሪዎች የትግራይን ህዝብ ከሌሎች ኢትዮጲያዊያን ጋር ለመነጠልና በጥርጣሬ እንዲተያይ የሚያደርጉትን ሴራ የትግራይ ህዝብ በዝምታ ማለፍ የለበትም፡፡
የትግራይ ህዝብ በተራ የህዉሃት ካድሪዎች ፕሮፖጋንዳ ከኢትዮጲያዊነቱ እንዲሸሽ የሚደረገዉን ሴራ በጥንቃቄ መረዳት አለበት፡፡ የትግራይ ህዝብ ጽኑ ፍላጎት ልማት፣ዴሞክራሲና ሰላም እንጂ ልዩነትና ጥላቻ አይድለም፡፡ ከህዉሃት የተለመደ የዉሸት ፕሮፖጋንዳ ያተረፈዉ ጥላቻና መከፋፈልን ነው፡፡
እድሜ ዘመናቸዉን የኢትዮጲያን ህዝብ ባይተዋር አድርገዉ የሃገርና የህዝብ ሃብት በመዝርፍ የናጠጠ ኑሮ የሚኖሩ የህዉሃት ካድሪዎች ዛሬም የትግራይን ህዝብ ከእኛ በላይ ላሳር በሚል አስተሳሰብ በተናጠል ሊሸነግሉት አይገባም፡፡
ላለፉት 30 እና 40 ዓመታት ወንበር ላይ ቁጭ ብለዉ የኖሩ የስርዓቱ ተላላኪ የነበሩ ግለሰቦችን ካሉበት እያፈላለጉ የትግራይን ህዝብ የድሮ ስርዓት ተመለሰ በሚል ከሌሎች ህዝቦች ጋር በጥርጣሬ እንዲተያይ አድርገዉ የስልጣን ዘመናቸዉን ማራዘም ይፈልጋሉ፡፡
በህዉሃት የስልጣን ዘመን ፍጹም ተግባራዊ ሲደረግ ያልነበረን የዉሸት ህገ መንግስትና የፌድራል ስርዓት ዛሬ ህገ መንግስቱ ተናደ፣ የፌድራል ስርዓቱ ፈረሰ በሚል አጉል መፈክር የትግራይን ህዝብ የፕሮፖጋንዳ መጠቀሚያ ማድረግ ተገቢነት የለዉም፡፡
የይስሙላ ፌድራሊዝም ስርዓት ዘርግቶ የኢትዮጲያን ህዝብ ከፋፍሎ እንደሉቡ ሲያደርግ የኖረዉ አምባገነን የህዉሃት ካድሪዎች ቡድን በኢትዮጲያ ህዝብ ለዉጥ ፈላጊነት ምክኒያት ተገፍተዉ መቀለ ከመሸገ በኋላም በዘረፈዉ ገንዘብ ሃገርንና ህዝብን ከማተራመስ አልታቀበም፡፡
ዛሬም በህዉሃት የሴራ ማንፌስቶ አስተሳሰብ የተቀረጹና በለዉጡ ምክኒያት ከስልጣን የተገለሉ ነባር የአማራና የኦሮሞ ሰዎችን ይዘዉ የፌድራሊዝምና ህገ መንግስታዊ ስርዓቱን ተጣሰ ሲሉ ይደመጣል፡፡ ይሁን እንጂ እነዚህ ሰዎች ህገ-መንግስቱም ይሁን የፌድራል ስርዓቱን እንኳን ሊያከብሩት ቀርቶ መኖሩን እንኳ አስበዉት አያዉቁም፡፡ እንዲህ ብለዉ ወመያየታቸዉ በራሱ ኢሉኝታ ማጣት ነዉ፡፡
በስልጣን ዘመናቸዉ ህገ መንግስቱ ቢከበር ኖሮ በርካታ ኢትዮጲያዊያን ቶርች አይደረጉም ነበር፡፡ ለአሰቃቂ ስርና እንግልት አይዳረጉም ነበር፡፡ የመብት አፈናም አይፈጸምባቸዉም ነበር፡፡ የነበረዉ ስርዓት ለባለጊዜዎች የተመቸ የይስሙላ ስርዓት ነው፡፡