Page 1 of 1

የብልጽግና ፓርቲ ያለ ምርጫ እስከ 2017 ይግዛ ማለት ስህተት ነው

Posted: 04 Jan 2020, 00:44
by Horus
የሲሳይ አጌና እና መሳይ መኮንን ፍርሃት ይገባኛል ።

ልክ እንዳሉት ሁከት፣ አመጽ፣ ግድያ ፣ ፍርሃት፣ ድምጽ ዘረፋ፣ ፓርቲ ክልከላ ሁሉ በልዩ ልዩ ቦታዎች ከትግሬ እስከ ባሌ እንደ ሚኖሩ ሁሉም ያምናል ።

ሁሉ ቢስማማ ለተወሰነ ግዜ ለምሳሌ አንድ አመት ቢገፋ ጥሩ ነበር ። ግን በ5 አመታት ይገፋ የሚለው ፍጹም ስህተት ነው ። ለምን?

አንድ፣ የ2012ቱ ምርጫ ተወደደም ተጠላም በቀውስ ታጅቦም ቢሆን አሸናፊ የሚሆነው ብልጽግና ፓርቲ ይሆናል ። ስለዚህ አቢይና ፓርቲው በገዥነት መቀጠላቸው አይቀሬ ነው ። ይህ ደሞ የነ ሲሳይን ፍርሃት ያስወግዳል ።

ሁለት፣ የምርጫው መደረግ ዋና እጅግ ጠቃሚ ትርፉ ሰላም በኢትዮጵያ ማምጣቱ አይደለም ። ሰላም የሚጸናው ምርጫ በመደረጉ ወይ አለ መደረጉ አይደለም ። ዎያኔዎች እና የዘር ጽንፈኞች ለውጥ መቃወማቸው ነው። እነዚህ ደሞ ተዳክመው እስካልከሰሙ ድረስ በቅድመ ምርጫም በድህረ ምርጫም ኢትዮዮጵያ ይኖራሉ ።

ሰልሆነም የምርጫው ትልቅ ፋይዳ ትልቅ የፖለቲካ ልምድና ትምህርት ይገኝበታል። ፓርቲዎች ይፈተኑበታል ። የጎሳም ሆነ የዜጋ ፖለቲካና ፓርቲዎች ይፈተኑበታል።

የምርጫ ቦርድ፣ ሚዲያ፣ ሲቪል ድርጅቶች ሁሉ ይማሩበታል፣ ይፈተኑበታል ።

ያለም ድርጅቶች ይገኙበታል።

ሶስት ። አሁን ያለው ዎያኔ ያስቀመጠው ፓርላማ ይለወጣል።

አራት ፣ ከብልጽግና ውጭ ያሉ ፓርቲዎች የተወሰኑ ወንበሮች አሸንፈው ፓርላማው አጓጊ የክርክር ቦታ ያደጉታል ።

አምስት፣ ገዚው ፓርቲ ራሱ የአምባ ገነንነት እምነት እንዳይይዝ ያደርገዋል ።

የ2012 ምርጫ እሰከነ ችግሩ ትልቅ የፖለቲካ ት/ቤት ሆኖ ያልፋል ። ዴሞክራሲ ሂደት ነው ። ሂደት የሚጀምረው እንደዚህ ነው ።

Re: የብልጽግና ፓርቲ ያለ ምርጫ እስከ 2017 ይግዛ ማለት ስህተት ነው

Posted: 04 Jan 2020, 14:48
by Horus