Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
simbe11
Member
Posts: 2088
Joined: 23 Feb 2013, 13:02
Location: Addis Ababa

ሰበር ዜና: በትግራይ ድብደባና እስር ተጀመረ

Post by simbe11 » 01 Jan 2020, 18:45

ሰበር ዜና: በትግራይ ድብደባና እስር ተጀመረ ብሎ ሰበር ዜና::
ድብደባና የግለሰቦች የገቡበት መጥፋት ዛሬ የተጀመረ ይመስል::
ህወሃት ላለፉት አርባ ምናምን አመታት ስትገድልና ስትዘትፍ እንደኖረች እየታወቅ ይህን ሰበር ዜና ብሎ ማቅረብ አይነፋም!!!


https://mereja.com/amharic/v2/192816

tarik
Senior Member+
Posts: 36293
Joined: 26 Feb 2016, 13:04

Re: ሰበር ዜና: በትግራይ ድብደባና እስር ተጀመረ

Post by tarik » 01 Jan 2020, 18:50

ሰበር ዜና: በትግራይ ድብደባና እስር ተጀመረ
January 1, 2020 – ውብሸት ታዬ — Comments ↓
Facebook
Twitter
Email
Share

በሕወሃት ተጠርቶ የነበረውና ‹‹የትግራይ ሕዝባዊ ኮንፍረንስ›› የተሰነው ጉባኤ ከተጠናቀቀ በኋላ በክልሉ መጠነ ሰፊ የሰብአዊ መብት ጥሰትና ከህግ አግባብ ውጪ የእስር እርምጃዎች እየተወሰዱ መሆኑን የአረና ትግራይ ለአንድነትና ለዴሞክራሲ ሊቀ መንበር የሆኑት አቶ አብርሃ ደስታ በተለይ ለመረጃ ቲቪ ገለጹ፡፡
እንደ አቶ አብርሃ አገላለጽ በጉባኤው ማጠናቀቂያ ላይ የሕወሃት ሊቀ መንበርና የትግራይ ክልል ምክትል መስተዳድር የሆኑት ዶ/ር ደብረጽዮን ገ/ሚካኤል ‹ድርጅታችንን በሚቃወሙ ሁሉ ላይ እርምጃ እንወሰወዳለን› ሲሉ ባወጁት መሰረት ድብደባና እስሩ ተጀምሯል ብለዋል፡፡

እስካሁን 21 የትግራይ ተወላጆች ላይ ከፍተኛ ድብደባ የተፈጸመ ሲሆን በትናንትናው ዕለት ደግሞ አቶ ሃደራ ወሉ እና አቶ መሀሪ ተክሌ በተባሉ ሁለት የአረና አባላት ላይ ድብደባ ከተፈጸመ በኋላ ለእስር እንደተዳረጉ ተገልጧል፡፡ ህወሃትን የሚቃወም በሙሉ ክልሉን ለቆ እንዲወጣ ጫና እየተደረገ መሆኑንም ሊቀ መንበሩ ተናግረዋል፡፡
አቶ አብርሃ የትግራይ ሕዝብ በአሁኑ ሰዓት በፍርሃት ተሸብቦ ከፍተኛ የሰብአዊ መብት ጥሰት እየተፈጸመበት እንደሆነ አስታውስው ከቀጣዩ ምርጫ ጋር በተያያዘ ፓርቲያቸው ዝግጅት እያደረገ ቢሆንም በተጨባጭ በትግራይ ምርጫ መደረጉ አጠራጣሪ እንደሆነባቸው ለመረጃ ቲቪ ገልጸዋል፡፡
Last edited by tarik on 01 Jan 2020, 18:54, edited 1 time in total.

Digital Weyane
Member+
Posts: 9834
Joined: 19 Jun 2019, 21:45

Re: ሰበር ዜና: በትግራይ ድብደባና እስር ተጀመረ

Post by Digital Weyane » 01 Jan 2020, 18:53

Tigray is the land of internationally recognized Human Rights activists like my Weyane brother Awash and myself. So how can there be human rights violations in a country that has championed human rights? It doesn't make any sense. We even respect the human rights of our domestic and wild animals in Tigray, let alone humans! :evil: :evil:

simbe11
Member
Posts: 2088
Joined: 23 Feb 2013, 13:02
Location: Addis Ababa

Re: ሰበር ዜና: በትግራይ ድብደባና እስር ተጀመረ

Post by simbe11 » 01 Jan 2020, 19:57

እኔን የገረመኝ ሰበር ዜና ምባሉ ነው:: ለ27 አመታት ሰውን ሲሰባብሩት ኖረው እንደ አዲስ::
ህወሃት የተለመደውን ድብደባ አጥብቆ እየገፋበት ነው ቢባል ያስኬዳል::

Post Reply