Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Horus
Senior Member+
Posts: 39844
Joined: 19 Oct 2013, 19:34

የተሳሳተው የኦሮሞ ውትድርና ኢንዱስትሪ ! 60 ሺ ልዩ ሃይል ለምን?

Post by Horus » 01 Jan 2020, 02:10

ሆረስ እባላለሁ፣ ቃል መሰንጠቅ አይመቸኝም ፣ ባንድ ቃል ይህው !

ማየት እስከሚያቅት ድረስ ብዙ ኦሮሞ ወጣቶች የወታደር ልብስ ለብሰው በረድፍ ተስልፈዋል ። እሺ ለምን?

ለወጣት ስራ ፈጠራ ።

አሁን ካሉት የኦሮሞ ፖሊሶች እና ወታደሮች ደምሩ ።

በኦሮሞ ያለው የስራ መስክ ውትድርና ብቻ የሆነ ይመስለኛል ። ይህ ደሞ ለኦሮሞ የረጅም ጊዜ ችግርና ቀውስ ነው ። ለምን?

አንደኛ፣ ወታደር አምራች ሃይል አይደለም ። ባሁን ዘመን በዘረፋ ወይ በወረራ መብላት ስለማይቻል ወታደር ሳይሰራ የሚቀለብ ህዝብ ነው። አርቀው ለማያስቡ የወታደር እና የፖሊስ ብዛት ህይል የሚሰጣቸው ይመስላቸዋል። ግዙፍ ስህተት !!

ይህ እጅግ መጥፎ ጎጂ ካልቸር ነው ።

ሁለትኛ ፣ ውትድርና የሚገባ ወጣት ሁሉ የማያድግ፣ የማይማር፣ የማይከብር፣ የማይሻሻል በመንግስት ተቀላቢ፣ የመንግስት ጥገኛ ኢንዱስትሪ ነው።

ኦሮሞ 60 ሺ የወጣት ወታደር ህዝብ ከመፍጠር 60 ሺ ወጣት የሚቀጥር አንድ ፋብሪካ ቢያቆሙ ብልህነት ነበር።

ሶስተኛ ፣ ወታደር ደሞ መጨረሻ ላይ የራሱን ህብረተሰብ ነው የሚበላ !

ሚሊተራይዘድ የሆኑ አገሮችን ታሪክ አስተውሉ ።

አራት፣ ወታደርና ፖሊስ የሚበዛበት (ሰርተው ማይበሉ) ቦታ በጉቦ፣ ሙስና፣ ሌብነት ፣ ወንጀል የሚበዛበት አገር ነው፣ ያ ነው ኦሮሞ የሚሆነው !!

ኬር