Page 1 of 1

በገብረ ጉራቻ በአራት ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ [BBC]

Posted: 06 Dec 2019, 08:21
by Revelations
Please wait, video is loading...

Re: በገብረ ጉራቻ በአራት ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ [BBC]

Posted: 06 Dec 2019, 08:27
by Revelations


በገብረ ጉራቻ ከተማ በታጣቂዎች በተከፈተ ተኩስ አራት የመንግሥት ጸጥታ አስከባሪ አባላት ላይ ጉዳት ደረሰ።

ትናንት (ሃሙስ) ምሽት 2፡30 ገደማ በሰሜን ሸዋ ዞን ኩዩ ወረዳ ገብረ ጉራቻ ከተማ የተፈጸመው ጥቃት ፖሊስ ጣቢያ ፊት ለፊት መሆኑን የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ደረጄ ደንደዓ ለቢቢሲ ተናግረዋል።

ጥቃቱ የመንግሥት የጸጥታ አስከባሪ አካላትን ለመግደል ያለመ መሆኑን አስተዳዳሪው ተናግረዋል።

የግድያ ሙከራው ኢላማ ከነበሩት መካከል የኩዩ ወረዳ ፖሊስ ኃላፊ ዋና ሳጅን አዱኛ ደቀባ እና አብረዋቸው የነበሩ ሌላ የወረዳው ፖሊስ አባል እንደሚገኙበት አስተዳዳሪው ይናገራሉ።

ጥቃቱ የተፈጸመው የፖሊስ አባላቱ እራት በልተው ወደ ፖሊስ ጣቢያ ግቢ እየገቡ ሳለ እንደነበር የሚናገሩት የኩዩ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ አቶ ደረጄ፤ በፖሊስ አባላቱ ላይ በሁለት አቅጣጫ ተኩስ እንደተከፈተባቸው ያስረዳሉ።

"ዋና ሳጅን አዱኛ እግራቸውን ነው የተመቱት። አብሯቸው የነበረው የፖሊስ አባል ደግሞ እጁን ነው የተመታው" የሚሉት ዋና አስተዳዳሪው፤ የተኩስ ድምጽ ሰምተው ወደ በስፍራው የተገኙ ሌሎች ሁለት የቀበሌ ሚሊሻዎች ላይም ተኩስ ተከፍቶ ጉዳት ደርሶባቸዋል" በማለት ትናንት ምሽት በገብረ ጉራቻ ከተማ የተፈጠረውን ክስተት ያስረዳሉ።

አቶ ደረጄ በአራቱም የጸጥታ አስከባሪ አካላት ላይ የደረሰው ጉዳት ለህይወት የሚያስጋ አለመሆኑን የተናገሩ ሲሆን፤ ሶስቱ እግራቸው ላይ አንዱ ደግሞ እጁ ላይ ጉዳት ማጋጠሙን አስረድተዋል።

"ሁለቱ በከተማችን በሚገኘው ሆስፒታል የህክምና ክትትል እየተደረገላቸው ሲሆን፤ ሁለቱ ደግሞ ለተጨማሪ ህክምና ወደ አዲስ አበባ ተልከዋል" ብለዋል።

በኩዩ ወረዳ ጸጥታ አከባሪዎች ላይ ያነጣጠሩ ጥቃቶች ሲፈጸሙ ይህ የመጀመሪያው አይደለም። የቀድሞ የወረዳው ፖሊስ ኃላፊ ጨምሮ ሁለት የፖሊስ አባላት ከወራት በፊት በታጣቂዎች በተተኮሰ ጥይት ተገድለዋል።

በተጨማሪም በወረዳው ቆላማ ቀበሌ ውስጥ ሁለት የቀበሌ ሚሊሻዎች ከሁለት ልጆቻቸው ጋር ተገድለው እንደነበር አስተዳዳሪው ያስታውሳሉ።

የኩዩ ወረዳ አስተዳዳሪ አቶ ደረጄ ለዚህ ሁሉ ወንጀል ተጠያቂ የሚያደርጉት "በቀድሞ የኦነግ ጦር ስር የነበሩ ታጥቀው የሚንቀሳቀሱ ታጣቂዎችን" ነው።

ትናንት ጥቃት ያደረሱት ታጣቂዎች ተከታትሎ መያዝ አለመቻሉትን የተናገሩት አስተዳዳሪው ፖሊስ የግድያ ሙከራውን እየመረመረ እንደሚገኝ ተናግረዋል።

https://www.bbc.com/amharic/news-506867 ... w_facebook

Re: በገብረ ጉራቻ በአራት ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ [BBC]

Posted: 06 Dec 2019, 09:00
by Revelations
Please wait, video is loading...

Re: በገብረ ጉራቻ በአራት ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ [BBC]

Posted: 06 Dec 2019, 09:48
by Digital Weyane
Tigray aka Singapore should deploy its peace-keeping forces to northern Shoa to restore law and order.

Re: በገብረ ጉራቻ በአራት ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ [BBC]

Posted: 06 Dec 2019, 11:57
by Za-Ilmaknun
Murdering government officials in that Region is now becoming a daily occurrence. This is very bad politics for those who genuinely aspire to promote the interests of their people and the country at large. In today's Ethiopia, the peaceful political venue is wide open if one has a winning political idea. Resorting to murdering officials is a road to no where. I am sure that the long hands of TPLF Nazis is behind all of these just so they can come back to Menilik Palace.

Re: በገብረ ጉራቻ በአራት ጸጥታ አስከባሪዎች ላይ የግድያ ሙከራ ተደረገ [BBC]

Posted: 06 Dec 2019, 13:43
by Revelations
Za-Ilmaknun wrote:
06 Dec 2019, 11:57
Murdering government officials in that Region is now becoming a daily occurrence. This is very bad politics for those who genuinely aspire to promote the interests of their people and the country at large. In today's Ethiopia, the peaceful political venue is wide open if one has a winning political idea. Resorting to murdering officials is a road to no where. I am sure that the long hands of TPLF Nazis is behind all of these just so they can come back to Menilik Palace.
AND OLF. It says it in the first report.