Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Hameddibewoyane
Member
Posts: 3890
Joined: 25 Sep 2019, 02:42

ከዚህ በላይ ምን ፌዝ አለ!

Post by Hameddibewoyane » 30 Nov 2019, 21:52

በትግራይ ክልል ያለው የኩናማ ብሄረሰብ ራሱን የሚያስተዳድርበት ዞን እንኳን አለው ወይ? ኢሮፕስ? ፣ እንደርታስ? ፣ ወጅራትስ? የቴምቤን አገውስ? ወልቃይትስ? ራያስ? ራሳቸውን በራሳቸው ያስተዳድራሉ? በክልሉ ጉዳይስ ህግ ያወጣሉ? ይሽራሉ?

ህሊና ካላችሁ የፌደራሊዝም እሳቤ አብይ ጉዳይ የሆነውን ራስን በራስ የማስተዳደር ጥያቄ መልሱ፡፡ ራሴን በራሴ ላስተዳድር የሚል ማህበረሰብ ጠባብ ፣ ጎጠኛ ፣ እያሉ ማሸማመቀቅ እና በዴሞክራሲያዊ ማዕከላዊነት መቀሌ የተወሰነውን ሌሎች ህዝቦች የሚቀበሉበት አሰራር አሃዳዊነት ይባላል፡፡

ትግሬ አይደለሁም የራሴ ማንነት አለኝ የሚለውን ህዝብ ዘረኛ እያሉ በቅኝ ግዛት እሳቤ መሰረት እየገዙ ፣ አዲስ ማንነት ለማስረፅ መሞከር ደግሞ #ጭፍላቂነት ይባላል፡፡

እውነታው ይሄው ነው!!!!!