-
- Senior Member+
- Posts: 34515
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
- Senior Member+
- Posts: 34515
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
-
- Senior Member+
- Posts: 34515
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Re: የጃዋር ፋይናንስ በክትትል ራዳር ውስጥ – ዳያስፖራ ደጋፊዎች ስለ ነገ አያውቁም!
ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ
ዓለምአቀፉ የፖሊስ መሥሪያ ቤት (ኢንተርፖል) እንደሚለው ከሆነ አሸባሪዎችን የማድረቂያው አንዱ መንገድ የገንዘብ እንቅስቃሴያቸውን መከታተል ነው። መ/ቤቱ አሸባሪዎችን በገንዘብ የመርጃ መንገዶች ብሎ የሚከተሉትን አስፍሯ፤ ዕርዳታ ከደጋፊዎች በማሰባሰብ፣ በማጭበርበር፣ ትርፍ አልባ ድርጅት በመመሥረትና አለአግባብ በድርጅቱ ስም መበልጸግ (OMN በአሜሪካ አገር በትርፍ አልባ ድርጅትነት የተመዘገበ መሆኑን ልብ ይሏል)፣ ሰዎችን አፍኖ በመውሰድና በምላሹ ካሣ በመጠየቅ፣ በሕገወጥ ንግድ በመሠማራት (ይህም በነዳጅ፣ በከሰል፣ በአልማዝ፣ በወርቅና በአደንዛዥ ዕጽ የሚጠቀልል ነው)።

ይህንን የገንዘብ (የዕርዳታ ድጋፍ) ማሰብሰብና ማዘዋወር ለመቆጣጠር በአገራት መካከል መረጃ የሚለዋወጥና ደረጃ የሚያወጣ Financial Action Taskforce (FATF) የሚባል ግብረኃይል ኢንተርፖል አለው። ከዚህ ግብረኃይል በተጨማሪ በዓለም ዙሪያ 164 የፋይናንስ ስለላ ዩኒት ያሉት Egmont Group የሚባል በመረጃ ልውውጥ የረቀቀ መስተጋብር (ኔትዎርክ) እንደሚጠቀም የኢንተርፖል ድረገጽ በግልጽ ያስረዳል። ይህ Egmont Group የተባለው ቡድን አሸባሪነትንና የገንዘብ ልውውጥን ለመከላከል የፋይናንስ ስለላ (financial intelligence) መረጃዎችን የሚያለዋውጥና የሙያ ዕገዛ የሚያደርግ መድረክ በማዘጋጀት የሚሠራ ቡድን ሲሆን ለአባል አገራት በአገራቸው ውስጥም ይሁን በአገራት መካከል በዓለምአቀፉ Anti Money Laundering and Counter Financing of Terrorism (AML/CFT) ውል መሠረት መረጃ በቀላሉ እንዲለዋወጡ የሚያደርግና የሚያስገድድም ነው።
በስምንት ቀጣናዎች በተደራጀው በዚህ የኢንተርፖል ቡድን በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ውስጥ ኢትዮጵያ ከረቡዕ July 3, 2019 (ሰኔ 26፤ 2011ዓም) ጀምሮ በአባልነት ተመዝግባ ትገኛለች።
ከዚህ በተጨማሪ ከመስከረም 1ዱ (ሴፕቴምበር 11) የአሸባሪዎች ጥቃት በኋላ የአሜሪካው የገንዘብ ሚኒስቴር የአሸባሪዎችን መስተጋብር ለይቶ የሚያወጣ፣ ሥር መሠረቱን የሚመረምርና የሚከታተል Terrorist Finance Tracking Program (TFTP) የሚባል መርሃግብር ዘርግቷል። ይህ መርሃግብር የአሸባሪዎችን የገንዘብ ምንጭና ፍሰት በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገራት የሚከታተል ሲሆን በቤልጂየም ከሚገኘው ዓለምአቀፉ የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ ልውውጥ ማኅበር Society for Worldwide Interbank Financial Telecommunication (SWIFT) በተጠርጣሪ አሸባሪዎች ላይ የፋይናንስ መረጃ የመጠየቅና የመሰብሰብ ሙሉ ፈቃድ አለው።
አሸባሪዎች የሚፈልጉትን ዓላማ ለማስፈጸም ገንዘብ ዋንኛ መሠረታቸው እንደሆነ የሚናገረው የካናዳው የገንዘብ ልውውጥና የዘገባ ትንተና ማዕከል (Financial Transactions and Reports Analysis Centre of Canada – FINTRAC) አሸባሪዎች ሕጋዊና ሕገወጥ የሆኑ የገንዘብ ምንጮችን እንደሚጠቀሙ ይናገራል። ከደጋፊዎችና አባላት የገንዘብ ዕርዳታ መሰብሰብ፣ ከግብረሰናይ ድርጅቶች ጋር አብሮ በመሥራት ገንዘብ ማስተላለፍ፣ በንግድ በመሠማራት ትርፍ በማግኘት ሕጋዊ የሚባሉትን መስመሮች የሚጠቀሙ ሲሆን በጦር መሣሪያ ዝውውር፣ በአደንዛዥ ዕጽ ዝውውር፣ በሕገወጥ የሰው ዝውውር፣ በግብር ማጭበርበር፣ ወዘተ ሕገወጥ የገንዘብ መሰብሰቢያ መንገዶች እንደሚጠቀሙ ማዕከሉ ያስረዳል።
በተለይ ከውጭ አገራት የሚሰበሰበው ገንዘብ ወደ አገር ውስጥ የሚገባበትን በተመለከተ አሸባሪዎች የተወሰነውን በህጋዊ የባንክ ዝውውር የሚጠቀሙ ሲሆን ሌላውን ግን በሐዋላ፣ በሁንዲ፣ በግለሰብ፣ በዕቃ ግዢ፣ በአካል በማዘዋወር፣ በወርቅና በመሳሰሉት በመቀየር፣ የተለያዩ ሕገወጥ ስልቶችን እንደሚጠቀሙ ማዕከሉ ይናገራል።
ይህንን መሰሉን የገንዘብ ዝውውር ከምንጩ፣ ከለጋሾቹ፣ ከተባባሪዎቹ ማንነት ጀምሮ እስከ መድረሻው ድረስ ለመከታተል የካናዳውም ሆነ የአሜሪካው እንዲሁም ኢንተርፖል ከየቤተእምነቱ፣ ከየስብሰባው አዳራሽና ሰልፍ የሚሰበሰቡ የምስል፣ የቪዲዮ ወዘተ መረጃዎችን እንዲሁም በየማኅበራዊ ሚዲያ የሚለጠፉ ፎቶዎችን፣ ቪዲዮዎችን፣ ጽሁፎችን ወዘተ በመሰብሰብ የሚጠቀሙ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። የካናዳው ማዕከል እንደሚለው ከሆነ አሸባሪነት በዓመጽና በኃይል ማኅበራዊ ጉዳት የሚያደርስ፣ ግልጽ የሆነ ማኅበራዊ ግፍ በመፈጸም የተጎጂዎችን ቁጥር የሚበራክት በመሆኑ በቁጥጥር ሥር ሊውል የሚገባው ወንጀል ነው ብሏል።
በእምነታቸውና በማንነታቸው ምክንያት መንግሥት በይፋ ባመነው መሠረት ሰማንያ ስድስት ዜጎች ከተገደሉ፣ ቤተ እምነቶች በእሳት እንዲጋዩ ከተደረገ በኋላ በአሜሪካ ስለ ቀጣዩ የትግል አቅጣጫና ለዚሁ ዓላማ ገንዘብ ለማሰባሰብ ወደ አሜሪካ ብሎም ወደ አውሮጳ ያቀናው ጃዋር መሀመድ ከተከታዮቹ ጋር በዓለም አቀፍ ደረጃ ሸምቀቆ ውስጥ መግባቱ ተሰማ። በኖርዌይ በልዩ ሁኔታ ክትትል መደረጉ ተመለከተ። በጀርመንና በእንግሊዝ ተመሳሳይ ክትትል እንደሚደረግ ታውቋል።
የጎልጉል ዜና አቀባዮች እንዳሉት ጃዋር በአሜሪካ ቆይታ ያካሄዳቸው ማናቸውም ተግባራት ከክትትል ነጻ አልነበረም። በተመሳሳይ በኖርዌይም ከአሜሪካ ጋር በጥምረት ይሁን በተናጠል ጃዋርና ዙሪያውን የከበቡት ሲጠኑ ነበር።
የንጹሃን መታረድ፣ የእምነት ቤቶች መቃጠል፣ ሰዎች በማንነታቸው ተለይተው መገደላቸውና ጃዋር ግንኙነት የሚያደርጋቸው አገሮች ጉዳይ ፊትለፊት ከሚታየው የታጋይነት ተግባር ጋር የማይጣጣሙ መሆናቸው ጃዋርና ባልደረቦቹ እንዲጠኑና በቅርበት እንዲመረመሩ ምክንያት እንደሆነ ነው የዜናው ሰዎች በጥቅሉ የተናገሩት።
ጃዋር በአሜሪካ የደረሰበት ተቃውሞ ምንም እንኳን መሪ አልባ፣ ያልተቀናጀ፣ ስድብ የታከለበት ቢሆንም ከሽብር መለያ ዓለምአቀፍ ስሞች ጋር ተያይዞ መወገዙና የተገደሉ ንጹሃን ምስል አደባባይ መቅረቡ ድንጋጤን ፈጥሯል። ኢንተርፖልና ሌሎች የጸረ ሽብር መሥሪያቤቶች ባላቸው ዓለምአቀፍ የአሸባሪነት መለኪያ መስፈርትም ድርጊቱ ሚዛን የሚደፋ መሆኑ ትኩረትን የሳበ ሆኗል።
ዜግነት እንደሚቀይር ከመናገሩ ውጪ በተግባር የኢትዮጵያ ዜግነት ስለመያዙ ይፋ ያላደረገው ጃዋር፣ በፍጹም ራስ መተማመን በማኅበራዊ ገጹ ላይ ተቃውሞው ጫና እንዳላሰደረበት ቢገልጽም በዲሲ የሃይማኖት መሪዎችን በመያዘና አብሯቸው ፎቶ በመንሳት፣ ቤተሰቦቹ ቤተክርስቲያን እንደገነቡ በመናገር ራሱን ከጽንፈኛ አካላት ለይቶ ለማሳየት ያደረገው ጥረት የፍርሃቻው አመላካች ተደርጎ ተወስዷል።
“ማኅበራዊ ሚዲያ የፖሊስ ምርመራ ሥራችንን አቃሎልናል። ወንጀለኞችን ለመለየት ከምንፈልገው በላይ መረጃ ከማኅበራዊ ገጻቸው ላይ በቀላሉ እናገኛለን” ሲሉ ከዚህ በፊት አንድ የአሜሪካ የምርመራ ቢሮ (ኤፍ.ቢ.አይ.) መርማሪ መናገራቸውን ያስታወሱት የዜናው ሰዎች፤ ጃዋር በሕግ የሚጠየቅበት አግባብ ከተጀመረ ስማቸውን እየቀየሩ ወይም እየደበቁ (anonymous እያሉ) ገንዘብ ሲሰጡና ይህንኑ ሲያስተባብሩ የነበሩ ሁሉ በምንም ዓይነት ሁኔታ እንደማያመልጡ አመልክተዋል። መረጃቸውን ከሕዝብ ዕይታ ቢያጠፉ ወይም ቢሰውሩ እንኳን በቀላሉ ወደኋላ ሄዶ ማግኘት እንደሚቻል የቴክኖሎጂው ባለሙያዎች ያስረዳሉ።
በአሜሪካ የሚኖሶታ ጠቅላይ ግዛት በርካታ የሶማሌ ክልል ተወላጆችና የሶማሌ ዜግነት ያላቸው በጃዋር ስብሰባ እንዲገኙና የገንዘብ ዕርዳታ እንዲያደርጉ ቢጠየቁም ወደፊት ከአሸባሪ ጋር ተባባሪ የመሆናቸው መረጃ በማስረጃ እንደሚቀርብባቸው በውስጥ ለውስጥ ስለደረሳቸው በስብሰባው ላይ ሳይገኙ መቅረታቸውን ስለ ጉዳዩ በቅርብ የሚያውቁ የጎልጉል ምንጮች ተናግረዋል።
ጎፈንድሚ (gofundme) ላይ ዕርዳታ የሚሰጡ ወገኖች ስማቸውን ያለመሙላት (anonymous እያሉ ገንዘብ የመስጠት) መብት ቢኖራቸውም ከየት ሰፈር፣ ከየትኛው ሞባይልና ኮምፒውተር፣ ከየትኛው ባንክና ከየትኛው አድራሻ ገንዘብ እንደላኩ አሁን በሚሠራበት ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ትብብር መሠረት መረጃቸው ስለሚገኝ የጃዋር አድሮም ቢሆን ወደ ሕግ መምጣት ከተከለከሉ የወንጀል ሕጎች (በተለይ አሸባሪነት) ጋር ተያይዞ በርካቶችን ሊያነካካ እንደሚችል ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ የሚገኙ የጎልጉል የዘወትር ተባባሪ ከፍተኛ ዲፕሎማት ገልጸዋል።
እርሳቸው እንዳሉት በአገራቸው (በአሜሪካ) የሕግ አካሄድና የምርመራ ሥራ በመጣደፍ የሚደረግ ባለመሆኑና መረጃ ፈርጥሞ እስኪደራጅ ድምጽ በማጥፋት ስለሚሠራ ቀኑ እስኪደርስ ጉዳዩ እንደ ቀለድ ይታያል፤ ምናልባትም ተባባሪ መስሎ የመታየት ሥራም ሊሠራ ይችላል። በሌላ አነጋገር “በረጅም ገመድ የታሰረች ዶሮ የተፈታች ይመስላታል” እንደሚባለው መሆኑ ነው።
የአሜሪካውን ጉዞ “አጠናቅቆ” ወደ ኖርዌይ ያቀናው ጃዋር፤ በኖርዌይ በተመሳሳይ አብረውት ካሉት ተባባሪዎቹ ጋር በድፍን ተጠንቷል፤ ግንዛቤም ተወስዷል። እንደ ታማኝ ዜና አቀባዮች ከሆነ ሁሉም ጉዳይ ተመዝግቧል፤ እርሱም በኖርዌይ ባደረገው ስብሰባ ባልተለመደ መልኩ በኦሮምኛ ለተጠየቀው በእንግሊዝኛ ሲሰጥ የነበረው “ከራሴው አንደበት ስሙኝ ንጹህ ሰው ነኝ” በማለት ራዳር ውስጥ ላስገቡት ሰዎች የተናገረው ተደርጎ ተወስዷል። በአሜሪካ የተጀመረው ፋይልን የማደራጀትና የማፈርጠሙ ሥራ ሲጠናቀቅ ጃዋር ወደ ህግ የሚቀርብ ከሆነ ከኖርዌይ፣ ከጀርመን፣ ከስዊድንና ከእንግሊዝ ወዘተ መረጃ የመለዋወጥ አሠራር አለ።
ጃዋር በተወለደበት አካባቢ አሁን በቅርቡ በርካታ ንጹሃን መታረዳቸው፣ ቤተ እምነቶችና አባቶች መገደላቸው አይዘነጋም። ጃዋር በቅድሚያ ኦሮሞ (ኦሮሞ ፈርስት) በሚለው ትግል ከመጠመዱ በፊት “እኔ በምኖርበት አካባቢ በሜንጫ ነው አንገቱን የምንለው” ሲል ባደባባይ መናገሩ አይዘነጋም።
ዓለምአቀፉ የፖሊስ መሥሪያ ቤት (ኢንተርፖል) እንደሚለው ከሆነ አሸባሪዎችን የማድረቂያው አንዱ መንገድ የገንዘብ እንቅስቃሴያቸውን መከታተል ነው። መ/ቤቱ አሸባሪዎችን በገንዘብ የመርጃ መንገዶች ብሎ የሚከተሉትን አስፍሯ፤ ዕርዳታ ከደጋፊዎች በማሰባሰብ፣ በማጭበርበር፣ ትርፍ አልባ ድርጅት በመመሥረትና አለአግባብ በድርጅቱ ስም መበልጸግ (OMN በአሜሪካ አገር በትርፍ አልባ ድርጅትነት የተመዘገበ መሆኑን ልብ ይሏል)፣ ሰዎችን አፍኖ በመውሰድና በምላሹ ካሣ በመጠየቅ፣ በሕገወጥ ንግድ በመሠማራት (ይህም በነዳጅ፣ በከሰል፣ በአልማዝ፣ በወርቅና በአደንዛዥ ዕጽ የሚጠቀልል ነው)።

ይህንን የገንዘብ (የዕርዳታ ድጋፍ) ማሰብሰብና ማዘዋወር ለመቆጣጠር በአገራት መካከል መረጃ የሚለዋወጥና ደረጃ የሚያወጣ Financial Action Taskforce (FATF) የሚባል ግብረኃይል ኢንተርፖል አለው። ከዚህ ግብረኃይል በተጨማሪ በዓለም ዙሪያ 164 የፋይናንስ ስለላ ዩኒት ያሉት Egmont Group የሚባል በመረጃ ልውውጥ የረቀቀ መስተጋብር (ኔትዎርክ) እንደሚጠቀም የኢንተርፖል ድረገጽ በግልጽ ያስረዳል። ይህ Egmont Group የተባለው ቡድን አሸባሪነትንና የገንዘብ ልውውጥን ለመከላከል የፋይናንስ ስለላ (financial intelligence) መረጃዎችን የሚያለዋውጥና የሙያ ዕገዛ የሚያደርግ መድረክ በማዘጋጀት የሚሠራ ቡድን ሲሆን ለአባል አገራት በአገራቸው ውስጥም ይሁን በአገራት መካከል በዓለምአቀፉ Anti Money Laundering and Counter Financing of Terrorism (AML/CFT) ውል መሠረት መረጃ በቀላሉ እንዲለዋወጡ የሚያደርግና የሚያስገድድም ነው።
በስምንት ቀጣናዎች በተደራጀው በዚህ የኢንተርፖል ቡድን በምስራቅና ደቡብ አፍሪካ ቀጣና ውስጥ ኢትዮጵያ ከረቡዕ July 3, 2019 (ሰኔ 26፤ 2011ዓም) ጀምሮ በአባልነት ተመዝግባ ትገኛለች።
ከዚህ በተጨማሪ ከመስከረም 1ዱ (ሴፕቴምበር 11) የአሸባሪዎች ጥቃት በኋላ የአሜሪካው የገንዘብ ሚኒስቴር የአሸባሪዎችን መስተጋብር ለይቶ የሚያወጣ፣ ሥር መሠረቱን የሚመረምርና የሚከታተል Terrorist Finance Tracking Program (TFTP) የሚባል መርሃግብር ዘርግቷል። ይህ መርሃግብር የአሸባሪዎችን የገንዘብ ምንጭና ፍሰት በአገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገራት የሚከታተል ሲሆን በቤልጂየም ከሚገኘው ዓለምአቀፉ የፋይናንስ ተቋማት የገንዘብ ልውውጥ ማኅበር Society for Worldwide Interbank Financial Telecommunication (SWIFT) በተጠርጣሪ አሸባሪዎች ላይ የፋይናንስ መረጃ የመጠየቅና የመሰብሰብ ሙሉ ፈቃድ አለው።
አሸባሪዎች የሚፈልጉትን ዓላማ ለማስፈጸም ገንዘብ ዋንኛ መሠረታቸው እንደሆነ የሚናገረው የካናዳው የገንዘብ ልውውጥና የዘገባ ትንተና ማዕከል (Financial Transactions and Reports Analysis Centre of Canada – FINTRAC) አሸባሪዎች ሕጋዊና ሕገወጥ የሆኑ የገንዘብ ምንጮችን እንደሚጠቀሙ ይናገራል። ከደጋፊዎችና አባላት የገንዘብ ዕርዳታ መሰብሰብ፣ ከግብረሰናይ ድርጅቶች ጋር አብሮ በመሥራት ገንዘብ ማስተላለፍ፣ በንግድ በመሠማራት ትርፍ በማግኘት ሕጋዊ የሚባሉትን መስመሮች የሚጠቀሙ ሲሆን በጦር መሣሪያ ዝውውር፣ በአደንዛዥ ዕጽ ዝውውር፣ በሕገወጥ የሰው ዝውውር፣ በግብር ማጭበርበር፣ ወዘተ ሕገወጥ የገንዘብ መሰብሰቢያ መንገዶች እንደሚጠቀሙ ማዕከሉ ያስረዳል።
በተለይ ከውጭ አገራት የሚሰበሰበው ገንዘብ ወደ አገር ውስጥ የሚገባበትን በተመለከተ አሸባሪዎች የተወሰነውን በህጋዊ የባንክ ዝውውር የሚጠቀሙ ሲሆን ሌላውን ግን በሐዋላ፣ በሁንዲ፣ በግለሰብ፣ በዕቃ ግዢ፣ በአካል በማዘዋወር፣ በወርቅና በመሳሰሉት በመቀየር፣ የተለያዩ ሕገወጥ ስልቶችን እንደሚጠቀሙ ማዕከሉ ይናገራል።
ይህንን መሰሉን የገንዘብ ዝውውር ከምንጩ፣ ከለጋሾቹ፣ ከተባባሪዎቹ ማንነት ጀምሮ እስከ መድረሻው ድረስ ለመከታተል የካናዳውም ሆነ የአሜሪካው እንዲሁም ኢንተርፖል ከየቤተእምነቱ፣ ከየስብሰባው አዳራሽና ሰልፍ የሚሰበሰቡ የምስል፣ የቪዲዮ ወዘተ መረጃዎችን እንዲሁም በየማኅበራዊ ሚዲያ የሚለጠፉ ፎቶዎችን፣ ቪዲዮዎችን፣ ጽሁፎችን ወዘተ በመሰብሰብ የሚጠቀሙ መሆናቸው የሚታወቅ ነው። የካናዳው ማዕከል እንደሚለው ከሆነ አሸባሪነት በዓመጽና በኃይል ማኅበራዊ ጉዳት የሚያደርስ፣ ግልጽ የሆነ ማኅበራዊ ግፍ በመፈጸም የተጎጂዎችን ቁጥር የሚበራክት በመሆኑ በቁጥጥር ሥር ሊውል የሚገባው ወንጀል ነው ብሏል።
በእምነታቸውና በማንነታቸው ምክንያት መንግሥት በይፋ ባመነው መሠረት ሰማንያ ስድስት ዜጎች ከተገደሉ፣ ቤተ እምነቶች በእሳት እንዲጋዩ ከተደረገ በኋላ በአሜሪካ ስለ ቀጣዩ የትግል አቅጣጫና ለዚሁ ዓላማ ገንዘብ ለማሰባሰብ ወደ አሜሪካ ብሎም ወደ አውሮጳ ያቀናው ጃዋር መሀመድ ከተከታዮቹ ጋር በዓለም አቀፍ ደረጃ ሸምቀቆ ውስጥ መግባቱ ተሰማ። በኖርዌይ በልዩ ሁኔታ ክትትል መደረጉ ተመለከተ። በጀርመንና በእንግሊዝ ተመሳሳይ ክትትል እንደሚደረግ ታውቋል።
የጎልጉል ዜና አቀባዮች እንዳሉት ጃዋር በአሜሪካ ቆይታ ያካሄዳቸው ማናቸውም ተግባራት ከክትትል ነጻ አልነበረም። በተመሳሳይ በኖርዌይም ከአሜሪካ ጋር በጥምረት ይሁን በተናጠል ጃዋርና ዙሪያውን የከበቡት ሲጠኑ ነበር።
የንጹሃን መታረድ፣ የእምነት ቤቶች መቃጠል፣ ሰዎች በማንነታቸው ተለይተው መገደላቸውና ጃዋር ግንኙነት የሚያደርጋቸው አገሮች ጉዳይ ፊትለፊት ከሚታየው የታጋይነት ተግባር ጋር የማይጣጣሙ መሆናቸው ጃዋርና ባልደረቦቹ እንዲጠኑና በቅርበት እንዲመረመሩ ምክንያት እንደሆነ ነው የዜናው ሰዎች በጥቅሉ የተናገሩት።
ጃዋር በአሜሪካ የደረሰበት ተቃውሞ ምንም እንኳን መሪ አልባ፣ ያልተቀናጀ፣ ስድብ የታከለበት ቢሆንም ከሽብር መለያ ዓለምአቀፍ ስሞች ጋር ተያይዞ መወገዙና የተገደሉ ንጹሃን ምስል አደባባይ መቅረቡ ድንጋጤን ፈጥሯል። ኢንተርፖልና ሌሎች የጸረ ሽብር መሥሪያቤቶች ባላቸው ዓለምአቀፍ የአሸባሪነት መለኪያ መስፈርትም ድርጊቱ ሚዛን የሚደፋ መሆኑ ትኩረትን የሳበ ሆኗል።
ዜግነት እንደሚቀይር ከመናገሩ ውጪ በተግባር የኢትዮጵያ ዜግነት ስለመያዙ ይፋ ያላደረገው ጃዋር፣ በፍጹም ራስ መተማመን በማኅበራዊ ገጹ ላይ ተቃውሞው ጫና እንዳላሰደረበት ቢገልጽም በዲሲ የሃይማኖት መሪዎችን በመያዘና አብሯቸው ፎቶ በመንሳት፣ ቤተሰቦቹ ቤተክርስቲያን እንደገነቡ በመናገር ራሱን ከጽንፈኛ አካላት ለይቶ ለማሳየት ያደረገው ጥረት የፍርሃቻው አመላካች ተደርጎ ተወስዷል።
“ማኅበራዊ ሚዲያ የፖሊስ ምርመራ ሥራችንን አቃሎልናል። ወንጀለኞችን ለመለየት ከምንፈልገው በላይ መረጃ ከማኅበራዊ ገጻቸው ላይ በቀላሉ እናገኛለን” ሲሉ ከዚህ በፊት አንድ የአሜሪካ የምርመራ ቢሮ (ኤፍ.ቢ.አይ.) መርማሪ መናገራቸውን ያስታወሱት የዜናው ሰዎች፤ ጃዋር በሕግ የሚጠየቅበት አግባብ ከተጀመረ ስማቸውን እየቀየሩ ወይም እየደበቁ (anonymous እያሉ) ገንዘብ ሲሰጡና ይህንኑ ሲያስተባብሩ የነበሩ ሁሉ በምንም ዓይነት ሁኔታ እንደማያመልጡ አመልክተዋል። መረጃቸውን ከሕዝብ ዕይታ ቢያጠፉ ወይም ቢሰውሩ እንኳን በቀላሉ ወደኋላ ሄዶ ማግኘት እንደሚቻል የቴክኖሎጂው ባለሙያዎች ያስረዳሉ።
በአሜሪካ የሚኖሶታ ጠቅላይ ግዛት በርካታ የሶማሌ ክልል ተወላጆችና የሶማሌ ዜግነት ያላቸው በጃዋር ስብሰባ እንዲገኙና የገንዘብ ዕርዳታ እንዲያደርጉ ቢጠየቁም ወደፊት ከአሸባሪ ጋር ተባባሪ የመሆናቸው መረጃ በማስረጃ እንደሚቀርብባቸው በውስጥ ለውስጥ ስለደረሳቸው በስብሰባው ላይ ሳይገኙ መቅረታቸውን ስለ ጉዳዩ በቅርብ የሚያውቁ የጎልጉል ምንጮች ተናግረዋል።
ጎፈንድሚ (gofundme) ላይ ዕርዳታ የሚሰጡ ወገኖች ስማቸውን ያለመሙላት (anonymous እያሉ ገንዘብ የመስጠት) መብት ቢኖራቸውም ከየት ሰፈር፣ ከየትኛው ሞባይልና ኮምፒውተር፣ ከየትኛው ባንክና ከየትኛው አድራሻ ገንዘብ እንደላኩ አሁን በሚሠራበት ዓለምአቀፍ የፋይናንስ ትብብር መሠረት መረጃቸው ስለሚገኝ የጃዋር አድሮም ቢሆን ወደ ሕግ መምጣት ከተከለከሉ የወንጀል ሕጎች (በተለይ አሸባሪነት) ጋር ተያይዞ በርካቶችን ሊያነካካ እንደሚችል ስማቸው እንዲጠቀስ ያልፈለጉ ዋሽንግተን ዲሲ አካባቢ የሚገኙ የጎልጉል የዘወትር ተባባሪ ከፍተኛ ዲፕሎማት ገልጸዋል።
እርሳቸው እንዳሉት በአገራቸው (በአሜሪካ) የሕግ አካሄድና የምርመራ ሥራ በመጣደፍ የሚደረግ ባለመሆኑና መረጃ ፈርጥሞ እስኪደራጅ ድምጽ በማጥፋት ስለሚሠራ ቀኑ እስኪደርስ ጉዳዩ እንደ ቀለድ ይታያል፤ ምናልባትም ተባባሪ መስሎ የመታየት ሥራም ሊሠራ ይችላል። በሌላ አነጋገር “በረጅም ገመድ የታሰረች ዶሮ የተፈታች ይመስላታል” እንደሚባለው መሆኑ ነው።
የአሜሪካውን ጉዞ “አጠናቅቆ” ወደ ኖርዌይ ያቀናው ጃዋር፤ በኖርዌይ በተመሳሳይ አብረውት ካሉት ተባባሪዎቹ ጋር በድፍን ተጠንቷል፤ ግንዛቤም ተወስዷል። እንደ ታማኝ ዜና አቀባዮች ከሆነ ሁሉም ጉዳይ ተመዝግቧል፤ እርሱም በኖርዌይ ባደረገው ስብሰባ ባልተለመደ መልኩ በኦሮምኛ ለተጠየቀው በእንግሊዝኛ ሲሰጥ የነበረው “ከራሴው አንደበት ስሙኝ ንጹህ ሰው ነኝ” በማለት ራዳር ውስጥ ላስገቡት ሰዎች የተናገረው ተደርጎ ተወስዷል። በአሜሪካ የተጀመረው ፋይልን የማደራጀትና የማፈርጠሙ ሥራ ሲጠናቀቅ ጃዋር ወደ ህግ የሚቀርብ ከሆነ ከኖርዌይ፣ ከጀርመን፣ ከስዊድንና ከእንግሊዝ ወዘተ መረጃ የመለዋወጥ አሠራር አለ።
ጃዋር በተወለደበት አካባቢ አሁን በቅርቡ በርካታ ንጹሃን መታረዳቸው፣ ቤተ እምነቶችና አባቶች መገደላቸው አይዘነጋም። ጃዋር በቅድሚያ ኦሮሞ (ኦሮሞ ፈርስት) በሚለው ትግል ከመጠመዱ በፊት “እኔ በምኖርበት አካባቢ በሜንጫ ነው አንገቱን የምንለው” ሲል ባደባባይ መናገሩ አይዘነጋም።