በኢህአዴግ መፍረስ ብቸኛው ተጎጂዎች የወያኔ ባለስልጣናት ብቻ ናቸው። / አቦ ተስፋዬ ገብረአብ
Posted: 15 Nov 2019, 11:12
የዘመናችን ኦሮሞ!
የኢህአዴግ መክሰም እና የ EPP መወለድ የኦሮሞን ህዝብ እንደሚጎዳው የሚገልጹ አስተያየቶች እያነበብኩ ነው። ሊገባኝ ያልቻለ አባባል ነው። ኢህአዴግ ቢዋሃድም ባይዋሃድም የኦሮሞ ህዝብ ቀዳሚ ጉዳይ ሊሆን አይችልም። የኦሮሞ ህዝብ ህልም እና ራእይ ለምን ከኢህአዴግ ጋር ይቆራኛል? ኢህአዴግን ታግሎ ለዛሬው ቀብር ያደረሰው ራሱ የኦሮሞ ህዝብ አይደለም እንዴ?
ከኢህአዴግ መፍረስ ጋር የኦሮሚያ ክልል ህልውና ሊያበቃለት አይችልም። እኔ እንደሚገባኝ ከኢህአዴግ መፈረስ ጋር የክልሎች ህልውና አብሮ ሊፈርስ አይችልም። የፌደራል ሲስተሙን ማፍረስም አይቻልም። በዚህ ጊዜ ኦሮሚያን አራት ቦታ ቆራርጦ "ኦሮሚያ" የሚለውን ስም ለመደምሰስ ታስቦ ከሆነ እብደት ነው። ይህን ማድረግ ይቻል የነበረበት ዘመን አልፎአል። ኦሮሚያን ቀርቶ ጃዋርን እንኩዋ መንካት እንደማይቻል ትናንት በይናችን አይተናል።
በመሆኑም በዚህ ጊዜ በኢህአዴግ መፍረስ ብቸኛው ተጎጂዎች የወያኔ ባለስልጣናት ብቻ ናቸው።
የኦሮሞ ህዝብ ከበቂ በላይ ኦሪጂናል መሪ ድርጅቶች አሉት። ድርጅቶቹ ቢቻል ተዋህደው ካልተቻለ ግንባር ሆነው የኦሮሞን ህዝብ ወክለው ኢትዮጵያን ለመምራት መዘጋጀት ብቻ ያለባቸው ይመስለኛል።
በተቀረ ኢህአዴግ አንድ ግንባር እንደመሆኑ የፈለገውን መሆን ይችላል። አባላቶቹ ይጨነቁበት። አባል ያልሆነ መብቱ ልክ እንደኔ አስተያየት መስጠት ብቻ ነው።
ወደድንም ጠላንም ይህን ለውጥ ያመጣው የኦሮሞ ወጣት እንደመሆኑ ህልም እና ራእይ አለው። ኢትዮጵያ ላይ ብቻ ሳይሆን መላ አፍሪቃ ቀንድ ላይ ተጽእኖ የማድረግ ብቃት አለው። ኦሮሞ በዚህ ዘመን አጋዥ እንጂ ታጋዥ አይደለም።
እና ወዳጆቼ ሆይ!
ባርኔጣችሁን አንስታችሁ ለመጨረሻ ጊዜ ኢህአዴግን ተሰናበቱት። "ኢህአዴግ" እንደ "ሶቪየት" አርጅቶ ሞቶአል። ወደ መቃብሩ ሲጉዋዝ ጥቂትም ቢሆን እንባ ማፍሰስ ግን ይገባል። ለሙዋች እንባ መጭመቅ ነባር ባህል ነውና!!
የኢህአዴግ መክሰም እና የ EPP መወለድ የኦሮሞን ህዝብ እንደሚጎዳው የሚገልጹ አስተያየቶች እያነበብኩ ነው። ሊገባኝ ያልቻለ አባባል ነው። ኢህአዴግ ቢዋሃድም ባይዋሃድም የኦሮሞ ህዝብ ቀዳሚ ጉዳይ ሊሆን አይችልም። የኦሮሞ ህዝብ ህልም እና ራእይ ለምን ከኢህአዴግ ጋር ይቆራኛል? ኢህአዴግን ታግሎ ለዛሬው ቀብር ያደረሰው ራሱ የኦሮሞ ህዝብ አይደለም እንዴ?
ከኢህአዴግ መፍረስ ጋር የኦሮሚያ ክልል ህልውና ሊያበቃለት አይችልም። እኔ እንደሚገባኝ ከኢህአዴግ መፈረስ ጋር የክልሎች ህልውና አብሮ ሊፈርስ አይችልም። የፌደራል ሲስተሙን ማፍረስም አይቻልም። በዚህ ጊዜ ኦሮሚያን አራት ቦታ ቆራርጦ "ኦሮሚያ" የሚለውን ስም ለመደምሰስ ታስቦ ከሆነ እብደት ነው። ይህን ማድረግ ይቻል የነበረበት ዘመን አልፎአል። ኦሮሚያን ቀርቶ ጃዋርን እንኩዋ መንካት እንደማይቻል ትናንት በይናችን አይተናል።
በመሆኑም በዚህ ጊዜ በኢህአዴግ መፍረስ ብቸኛው ተጎጂዎች የወያኔ ባለስልጣናት ብቻ ናቸው።
የኦሮሞ ህዝብ ከበቂ በላይ ኦሪጂናል መሪ ድርጅቶች አሉት። ድርጅቶቹ ቢቻል ተዋህደው ካልተቻለ ግንባር ሆነው የኦሮሞን ህዝብ ወክለው ኢትዮጵያን ለመምራት መዘጋጀት ብቻ ያለባቸው ይመስለኛል።
በተቀረ ኢህአዴግ አንድ ግንባር እንደመሆኑ የፈለገውን መሆን ይችላል። አባላቶቹ ይጨነቁበት። አባል ያልሆነ መብቱ ልክ እንደኔ አስተያየት መስጠት ብቻ ነው።
ወደድንም ጠላንም ይህን ለውጥ ያመጣው የኦሮሞ ወጣት እንደመሆኑ ህልም እና ራእይ አለው። ኢትዮጵያ ላይ ብቻ ሳይሆን መላ አፍሪቃ ቀንድ ላይ ተጽእኖ የማድረግ ብቃት አለው። ኦሮሞ በዚህ ዘመን አጋዥ እንጂ ታጋዥ አይደለም።
እና ወዳጆቼ ሆይ!
ባርኔጣችሁን አንስታችሁ ለመጨረሻ ጊዜ ኢህአዴግን ተሰናበቱት። "ኢህአዴግ" እንደ "ሶቪየት" አርጅቶ ሞቶአል። ወደ መቃብሩ ሲጉዋዝ ጥቂትም ቢሆን እንባ ማፍሰስ ግን ይገባል። ለሙዋች እንባ መጭመቅ ነባር ባህል ነውና!!