አንዳንድ ሚዲያዎች ወልደያ የሞቱት ተማሪዎች ቁጥር ማነስ አበሳጭቷቸዋል!
Posted: 11 Nov 2019, 09:23
ዛሬ ጥዋት የኦኤም ኤኑ ( OMN) ጋዜጠኛ ደጀኔ ጉተማ ወደ ወልደያ ዩኒቨርሲቲ ያሉ ተማሪዎች ደውሎ፤ “የሞቱት ተማሪዎች ብዙ ናቸው ይባላል አንተ ያየኸው ስንት ነው?” ይለዋል ተማሪውም “2 ብቻ ናቸው” አለው፡፡ ደጀኔም ተናዶ “እንዴት ሁለት ብቻ ይሆናል በደንብ ፈልጋችሗል ወደ ጫካ የተጣለ የለም?” አለው፡፡ ተማሪውም “የለም” አለው፡፡ “የቆሰሉስ ስንት ይሆናሉ?” አለ ደጀኔ በንዴት “10 ይሆናሉ” “እንዴት አንተ መረጃ የለህም ማለት ነው እኛ የሰማነው ከ50 በላይ ነው::” ሲለው ተማሪውም “እረ እኔ ዞሬ አይቻለሁ 10 ነው” አለው፡፡
ደጀኔም “ተመልካቾቻችን የሟቾች ቁጥር ይጨምራል ብለን ተስፋ በማድረግ በጉጉት እየጠበቅን ነው እንደደረሰን እንግልጽላችሗለን” ብሎ ተሰናበተ፡፡ እንዲህ በሰዎች ህዎት መነገድ ነው አንግዲህ የኛ ሀገር ሚዲያ እና ፖለቲከኞች የተያያዙት፤ ሞት እረከሰ አሁን ሞቱ ሳይሆን አገዳደሉ ሆኗል ሚዲያ የሚስበው፡፡ ለማንኛውም የሞቱትን ልጆች ነፍሳቸውን በገነት ያስቀምጥልን እላለሁ ለቤተሰባቸውም መጽናናትን ይስጥልን"

ደጀኔም “ተመልካቾቻችን የሟቾች ቁጥር ይጨምራል ብለን ተስፋ በማድረግ በጉጉት እየጠበቅን ነው እንደደረሰን እንግልጽላችሗለን” ብሎ ተሰናበተ፡፡ እንዲህ በሰዎች ህዎት መነገድ ነው አንግዲህ የኛ ሀገር ሚዲያ እና ፖለቲከኞች የተያያዙት፤ ሞት እረከሰ አሁን ሞቱ ሳይሆን አገዳደሉ ሆኗል ሚዲያ የሚስበው፡፡ ለማንኛውም የሞቱትን ልጆች ነፍሳቸውን በገነት ያስቀምጥልን እላለሁ ለቤተሰባቸውም መጽናናትን ይስጥልን"
