Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34434
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Post
by Revelations » 31 Oct 2019, 16:56
አዲስ አበባ (ፋና) – ከጥቅምት 11 ቀን፣ 2012 ዓ.ም. ክስተት ጋር ተያይዞ ግጭት በመቀስቀስ የተጠረጠሩ 409 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት አስታወቀ።
የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥቅምት 20 ቀን፣ 2012 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው ላይ በወቅቱ በነበረው ግጭት የ78 ዜጎች ሕይወት ማለፉን አንስተዋል።
በወቅቱ በግጭቱ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የፀጥታ መዋቅሩ በሙሉ አቅሙ መሥራቱንም ነው የገለፁት። የጸጥታ አካላት ችግሮች በተፈጠሩባቸው አካባቢዎች እስከ ሕይወት መስዋዕትነት በመክፈል ለማረጋጋት እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል።