Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Revelations
Senior Member+
Posts: 34434
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

ሰው በተጨፈጨፈበት ምድር "ግጭት" ብሎ የሚተርክ መንግስት ላይ ደርሰናል

Post by Revelations » 31 Oct 2019, 16:56

አዲስ አበባ (ፋና) – ከጥቅምት 11 ቀን፣ 2012 ዓ.ም. ክስተት ጋር ተያይዞ ግጭት በመቀስቀስ የተጠረጠሩ 409 ሰዎች በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ፅሕፈት ቤት አስታወቀ።

የጠቅላይ ሚኒስትር ፅህፈት ቤት ፕሬስ ሴክሬታሪ ጽህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ንጉሱ ጥላሁን በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ ጥቅምት 20 ቀን፣ 2012 ዓ.ም. ከሰዓት በኋላ መግለጫ ሰጥተዋል። በመግለጫቸው ላይ በወቅቱ በነበረው ግጭት የ78 ዜጎች ሕይወት ማለፉን አንስተዋል።

በወቅቱ በግጭቱ ሊደርስ የሚችለውን ጉዳት ለመቀነስ የፀጥታ መዋቅሩ በሙሉ አቅሙ መሥራቱንም ነው የገለፁት። የጸጥታ አካላት ችግሮች በተፈጠሩባቸው አካባቢዎች እስከ ሕይወት መስዋዕትነት በመክፈል ለማረጋጋት እየሰሩ መሆኑን አንስተዋል።

Revelations
Senior Member+
Posts: 34434
Joined: 06 Jan 2007, 15:44

Re: ሰው በተጨፈጨፈበት ምድር "ግጭት" ብሎ የሚተርክ መንግስት ላይ ደርሰናል

Post by Revelations » 31 Oct 2019, 17:11



Post Reply