


አብይ አህመድ የተናገረው ሲተረጎም የሚከተለው ነው
"በፓርላማ ንግግር ባደረግሁበት ጊዜ የሆነ አባባል ተጠቅሜ ነበር። "ስኮርት ሀገር ያላችሁ" ብዬ ነበር። አስታወሳችሁ?
"ስኮርት" በሀገራችን በጂማ መጠባበቂያ ጎማ ማለት ነው። ታውቃላችሁ አይደል። ለካስ በነጃዋር ሀገር ስኮርት ማለት ጥበቃ ማለት ነው። እሱ የመሰለው "ጥበቃ ያላችሁ ሰዎች" ብሎ ነው የተረዳው (ሳቅ)።
እየሰማችሁኝ ነው? ሆኖም እንደዚያስ ቢባል? አልገባችሁም?
"አዎ" (ተሰብሳቢው)
ፓርላማ ላይ በተናገርኩ ጊዜ "ስኮርት ሀገር ያላችሁ ሰዎች" ብዬ ነበር። ሁለተኛ (መጠባበቂያ) ሀገር ማለቴ ነበር።
ገባችሁ?
"አዎ"።
ስኮርት ማለት የመኪና ጎማ ሆኖ ሌላው ጎማ ሲፈነዳ የሚቀየር መጠባበቂያ ትርፍ ጎማ ማለት ነው። "ትርፍ ሀገር ያላችሁ" ማለቴ ነበር። በነጃዋር ሀገር ግን ስኮርት ማለት የፖሊስ ጥበቃ ማለት ነው።
እየሰማችሁኝ ነው?"