
ክቡር አቶ ኢሳያስ አፈውሪቄ የኤርትራ ፕሬዝዳንት
የትህነግ መራሹ መንግስት የተለመደውን ከስብሰባ ማዕግስት የሚያውጣውን የአስመሳይነት መግለጫ ያደገበት የመሰሪነት ባህሪው ነው፡፡
ባለፋት ሃያ ዓመት በዚህ የመሰሪነት ተፈጥሮው የአንድ እናት ልጆችን በማለያየት የኢትዮጵያ እና የኤርትራን ህዝብ በመግለጫ በመሽንገል በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ መንግስታዊ የጥፋት ሥራ ሲሰራ መቆይቱ የአለም የአደባባይ ሀቅ ነው፡፡
በህዝብ ትግል ሀጢያት ከሚሰራበት በተር ስልጣን የተወገድ ቢሆን ሀገሪቱ ሰላማዊ ሆና ያላትን ተፈጥሮዊ ፀጋ ከራሷ አልፋ ለሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች
እንዳትተርፍ በተልዕኮ የተለመደውን የማተራመስ እና ከእኔ በላይ ለአሳር ነው የሚል ግትርነት ከአንድ ዓመት በመያዝ ሲደመር እና ሲቀነስ እንደቆይ ለኤርትራ ህዝብ የተሰውር አይደለም፡፡
እውነታው ይህ ሆኑ እያለ በተደጋጋሚ ከስብሰባ ማዕግስት በተለመደው የመሰሪነት ባህሪ የሚሰጥ መግለጫ ለኤርትራ ህዝብ ሰሚ እና ተቀባይነት የሌለው የገደል ላይ ጭኾት ነው፡፡
“ ድመት መልኮሳ አመሏን አትረሳ ” አለ አማራ እውነቱን እኮ ነው፡፡መቺም ቢሆን በተለያዩ ሀገሮች አምባሳደራት እና የሀገር መሪዎች የሚደረግ መርህ አልባ
ሽምግልና የፓርቲ መግለጫ የባህታዊ ቀበሮ ባህሪ በመሆኑ ተቀባይነት የሌለው ለኤርትራ ህዝብ ውሃ የማይቋጥር ተግባር እና ሀሳብ ነው፡፡
ምክንያቱም
1ኛ./ የእኛ በመርህ ላይ የተመሰረተው ግንኙነታችን ከክልል መንግስት ጋር ሳይሆን ከፌድራል መንግስት ጋር ነው፡፡
2ኛ/ ምንም እንኳን የትግራይ ህዝብ ከህዝባችን ጋር የቋንቋና የባህል ተመሳሳይነት ቢኖርውም መሪ ድርጅቶ ትህነግ አብሮት ለታገለው ለአማራ ህዝብ ያልሆነ ለኤርትራ ህዝብ ይበጃል ብልን አናምነም፡፡
3ኛ/ባለፈው ሃያ ዓመት በትህነግ መሰሪነት የኤርትራ ህዝብ ከሁለተኛ ሀገሮ በመሰሪው ትህነግ ትንኩል ሀብት ንብረታችውን ጥለው ሲፈናቀሎ ባለማተቡ የአማራ ህዝብ “ያሉት ከሚጠፋ የወለዱት ይጥፋ ” በማለት የህዝባችን ንብረት እና ሀብት መልሷል፡፡
በመሆኑ ትህነግ የአማራን ህዝብ ጠላት በማድረግ በደል ያደረሰበት በመሆኑ ይቅርታ ሳይጠይቅ ከአማራ ጠላት ጋር ህብረት አንመሰረትም፡፡
4ኛ/ ትህነግ ከእኔ በላይ ላሳራ የሚል የማያረጅ ግትርነት ባህሪው ጋር ያለፍቺ የተጋባ በመሆኑ ለጋራ ተጠቃሚነት እና እኩልነት አለርጂ ነው፡፡
ሰለሆነም ለጊዜያው ትዳር ብልን ከኢትዮጵያ ህዝብ ጋር የጀመረነው አዲስ ህብረት በምንም ታምር አናደናቅፍም፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ እና የኤርትራ ህዝብ አብሮነት በቀበሮ ባህታዊ መግለጫ እና መርህ አልባ የሽምግልና ጋጋታ አይደናቀፍም፡፡
ክቡር አቶ ኢሳያስ አፈውሪቄ የኤርትራ ፕሬዝዳንት
አስመራ