ሰንደቃላማችን የሉአላዊነታችን መገለጫ ነው
*ሰንደቅ ዓላማ ሀገራችን የተመሠረተችባቸውን እርስ በርስም ሆነ ከሌሎች ጋር የሚያገናኙንን እሴቶች ሁሉ የሚያሳይ ነው፤
* እኔ ባደግኩባት ኢትዮጵያ ሰንደቅ ዓላማ ሲሰቀልም ሆነ ሲወርድ ዜጎች ቆመው የሚያከብሩት ነበር፤ የዛሬው ቀን ለሰንደቅ ዓላማችንን ክብር መመለስ የሚችል መሆን አለበት፤
* ለልጆቻችን የሰንደቅ ዓላማን ክብር እናስተምር
* ሰንደቅ ዓላማችን የአንድነታችን መገለጫ እንጂ በፖለቲካ ምክንያት የልዩነታችን መገለጫ መሆን የለበትም
* ብሔራዊ ሰንደቅ ዓላማችን ሲውለበለብ ከክልል አርማዎች ሁሉ ከፍ ብሎ የሚታይ መሆን አለበት
* አትሌቶቻችን ሰንደቅ ዓላማችንን ከፍ አድርገው በማሳየት ነው ክብራችንን የሚገልጹት
*ሀገራችን ኢትዮጵያ ጀግኖችን ትፈልጋለች፣ ግጭትን የሚደግሱ ሳይሆኑ የሰላምን ውድነት የሚሰብኩ፣ ልዩነትን ሳይሆን አንድነትን የሚሰብኩ፣ ሀገሬን የሚሉ ዜጎችን ትፈልጋለች
* እልፍ አዕላፍ የተሰዉላትን ሰንደቅ ዓላማ እኛ ዛሬ አንድ ሆነን ብዙ ተዓምሮችን እንሥራላት
* የክብራችን መገለጫ የሆነው ሰንደቅ ዓላማ ለዘለዓለም ከፍ ብሎ ይውለብለብ!