Page 1 of 1

በኢትዮጵያ ውስጥ አንድም ማህበራዊ ፈላስፋ (ሶሺያል ፊሎሶፈር) እንደሌለ ሁሉ አንድም የባህል ሊቅ የለም !

Posted: 04 Oct 2019, 22:39
by Horus
ይህን ለማለት ያስገደደኝ የማነበውና የማየው ሁሉ ወይ የፖለቲካ ብሽሽቅ ወይ ደሞ ሁሉም ነገር የህይል ፉክከር መሳሪያ ለማደግ መሞከር ነው። ባህል ተበልው ሰው የሚንጋጋላቸው ክንውኖች ሁሉ አንድም ሰው ምን እንደ ሆኑ ከሶሺያ ሳይኮልጂም ሆነ ከፖለቲካል ሳይኮሎጂ ጋር አገናዝቦ የሚገጽ ሰው የለም፤ ማለትም ከሚሰለፉት ሁሉ ማለት ነው። እኔ ከማየው አብዛኛው በዘልማድ የሚከወን ጋጋታ እንጂ በውስጡ ይህ ነው ሚባል የእምነት ፍልስፍና፣ ወይ የባህል ዘይቤና ክህሎት ወይ ሌላ ማህበራዊ እሴትም ሆነ ንድፈ ሃሳብ አላይበትም ። እኔ ማየው ዝም ብሎ የፖለቲካ ርኩቻ ነው። ያ ደሞ የሚከናወነው በኢሬቻም በገዳም አይደለም፣ በፖለቲካ አደረጃጀት ነው ።

Re: በኢትዮጵያ ውስጥ አንድም ማህበራዊ ፈላስፋ (ሶሺያል ፊሎሶፈር) እንደሌለ ሁሉ አንድም የባህል ሊቅ የለም !

Posted: 04 Oct 2019, 23:25
by Horus
ለምሳሌ ዛሬ ያይሁት ነገር አለ። ዛፉ ይሳማል፣ መሪቱም ይሳማል ። ይህም ማለት ዛፉ እንደ ቤት እግዚአብሄር ሆኖ የመንፈስ ማደሪያ ነው ማለት ነው ። ያ ከሆነ ደሞ በአሉ ቢያንስ ሃይማኖታዊ በበዛ መንፈሳዊ መሆኑ ነው። ያ ግ ን በተግባር አይታይም ።የሚታየው እንደ መንግስቱ ዘመን የፖሊታከ ወጠጤነት ነው። ማህበራዊ በአል ነው እንዳይባል ደሞ ያደባባይ ተይንት ነው ። ያም ሆነ ያ አንድ እምነትም ሆነ ባህል እውነተኛ ለመሆን ብዙ ዘመን መደጋገም ሳልለበት እና ከጊዜው ጋር እየተከለሰ ስለሚሄድ ለእኔ ይህ ሁሉ የጃዋር እንቶኔ ግርግር ነው ።