"የህወሃት የስልጣን ዘመን የተሟሸው አማራው በበደኖ እና አርባጉጉ ባሰማው የሲቃ ድምፅ ነው"
Posted: 27 Sep 2019, 14:05
"የዛሬዋን ኢትዮጵያ በስሁት መንገድ እየነዳ አምጥቶ ገሃነም በር ላይ አስቀምጦ የሄደው የህወሃት ዋና ፈሊጥ አማራ የሚባለውን የኢትዮጵያ ህዝብ በሆነውም ባልሆነውም መክሰስ፣ ማክፋፋት፣ ቅስም መስበር ነው፡፡ ህገ-መንግስት ሲፅፍ የአማራውን ትምክህት ለመስበር እንደሆነ ለተላላ ሰሚዎቹ ይነግራል;
የመሬትን ባለቤትነት ለብሄር ብሄርሰቦች ሰጠሁ ሲል መሬቱን አማራ እንዳይገዛው እየጠበቅኩላችሁ ነው ሲል እየሰበከ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ አማራው ንጉስ የጠላው ፍጡር የሚያየውን መከራ ሁሉ አይቷል፡፡የህወሃት የስልጣን ዘመን የተሟሸው አማራው በበደኖ እና አርባጉጉ ባሰማው የሲቃ ድምፅ ነው፡፡ይህ የሲቃ ድምፅ ለህወሃት የድል ማህተም ነው፤ የአማራ አከርካሪ መሰበር፣ ላይመለስ ሞቶ ርቆ መቀበር ምልክት ነው፡፡ የሰው ልጅ አሰቃቂ ሞት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ መሆኑ ቀርቶ የዝቅተኝነት ስሜት ማርገቢያ ሙዚቃ ሆነ፡፡ የአማራው መፈናቀል፣ በአንድ ሌሊት ሃብት ንብረት አራግፎ ነፍስ ብቻ ይዞ እግር ወደመራው መትመም አጀብ የማያሰኝ አዘቦታዊ ነገር፣ ጆሮ ዳባ ልበስ የሚባል ተገቢ ነገር መሰለ፡፡ ይህ የሆነው ለአጭር ጊዜ አይደለም-ለሩብ ምዕተዓመት እንጅ!
በሃገራችን መፈናቀል ብርቅ ሆኖ ማነጋገር የጀመረው ከሁለት አመት ወዲህ፣ የዘር ፖለቲካው ከአማራው ሌላ ብሄረሰቦችን ቤት ማንኳኳት ሲጀምር ነው፡፡የዘውግ ፖለቲካው ከጨቋኙ የአማር ብሄር በስተቀር ሌሎች ብሄር ብሄረሰቦችን አስተቃቅፎ የሚያኖር፣ ከአማራ ጭቆና የሚታደግ ድንቅ እድል ተደርጎ ሲሰበክ ኖሯል፡፡ የዘውግ ፌደራሊዝሙ ለአማራው ያልተመቸው ደግሞ ሊጨቁን በሃገር ዳርቻ ስለተበተነ ነው የሚል ተረክ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ሲተረክ ኖሯል፡፡ ይህ ተረክ እውነት አለመሆኑ እየታየ የመጣው በጨቋኝነት የማይታወቁት እንደ ጌዲኦ፣ ኦሮሞ ከሶማሌ ክልል፣ ከምባታ ከከፋ፣ ወላይታ ከሲዳማ በገፍ መፈናቀል ሲጀምሩ ነው፡፡ የሆነ ሆኖ ይህ እውነታ የታወቀው እጅግ ዘግይቶ በመሆኑ አማራው ከብዙ አቅጣጫ በሚወረወር ጦር እንዲዋከብ አድርጎት ኖሯል፡፡ የዚህ ድምር ውጤት ዛሬ በአስፈሪ ሁኔታ እያደገ የመጣውን የአማራ ብሄርተኝነት ወልዷል፡፡" Meskerem Abera
https://ethiothinkthank.com/2019/09/25/ ... tionalism/
የመሬትን ባለቤትነት ለብሄር ብሄርሰቦች ሰጠሁ ሲል መሬቱን አማራ እንዳይገዛው እየጠበቅኩላችሁ ነው ሲል እየሰበከ ነው፡፡ በዚህ ሁሉ ውስጥ አማራው ንጉስ የጠላው ፍጡር የሚያየውን መከራ ሁሉ አይቷል፡፡የህወሃት የስልጣን ዘመን የተሟሸው አማራው በበደኖ እና አርባጉጉ ባሰማው የሲቃ ድምፅ ነው፡፡ይህ የሲቃ ድምፅ ለህወሃት የድል ማህተም ነው፤ የአማራ አከርካሪ መሰበር፣ ላይመለስ ሞቶ ርቆ መቀበር ምልክት ነው፡፡ የሰው ልጅ አሰቃቂ ሞት የሰብዓዊ መብት ጉዳይ መሆኑ ቀርቶ የዝቅተኝነት ስሜት ማርገቢያ ሙዚቃ ሆነ፡፡ የአማራው መፈናቀል፣ በአንድ ሌሊት ሃብት ንብረት አራግፎ ነፍስ ብቻ ይዞ እግር ወደመራው መትመም አጀብ የማያሰኝ አዘቦታዊ ነገር፣ ጆሮ ዳባ ልበስ የሚባል ተገቢ ነገር መሰለ፡፡ ይህ የሆነው ለአጭር ጊዜ አይደለም-ለሩብ ምዕተዓመት እንጅ!
በሃገራችን መፈናቀል ብርቅ ሆኖ ማነጋገር የጀመረው ከሁለት አመት ወዲህ፣ የዘር ፖለቲካው ከአማራው ሌላ ብሄረሰቦችን ቤት ማንኳኳት ሲጀምር ነው፡፡የዘውግ ፖለቲካው ከጨቋኙ የአማር ብሄር በስተቀር ሌሎች ብሄር ብሄረሰቦችን አስተቃቅፎ የሚያኖር፣ ከአማራ ጭቆና የሚታደግ ድንቅ እድል ተደርጎ ሲሰበክ ኖሯል፡፡ የዘውግ ፌደራሊዝሙ ለአማራው ያልተመቸው ደግሞ ሊጨቁን በሃገር ዳርቻ ስለተበተነ ነው የሚል ተረክ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ሲተረክ ኖሯል፡፡ ይህ ተረክ እውነት አለመሆኑ እየታየ የመጣው በጨቋኝነት የማይታወቁት እንደ ጌዲኦ፣ ኦሮሞ ከሶማሌ ክልል፣ ከምባታ ከከፋ፣ ወላይታ ከሲዳማ በገፍ መፈናቀል ሲጀምሩ ነው፡፡ የሆነ ሆኖ ይህ እውነታ የታወቀው እጅግ ዘግይቶ በመሆኑ አማራው ከብዙ አቅጣጫ በሚወረወር ጦር እንዲዋከብ አድርጎት ኖሯል፡፡ የዚህ ድምር ውጤት ዛሬ በአስፈሪ ሁኔታ እያደገ የመጣውን የአማራ ብሄርተኝነት ወልዷል፡፡" Meskerem Abera
https://ethiothinkthank.com/2019/09/25/ ... tionalism/