https://www.vaticannews.va/ti/church/ne ... zione.html
ሃገረ ኤርትራ - ናብ ኣቶ ሰመረ ርእሶም - ሚንስተር ትምህርቲ - ኣሥመራ።
ኣሥመራ 04.09.2019 (፳፱ ነሓሰ ፳፻፲፩ ዓ. ም. )
ጕዳይ፦ ብመንግሥቲ ዝተወስደ ናይ ቤተክርስትያን ኣብያተ ትምህርቲ
1. ንሕና ጳጳሳት ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን፣ ንሃገርና ኮነ ንኵነታት ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ኣብ ሃገርና ብዚርኢ፣ ምስ ኣካላት መንግሥቲ ተራኺብና ክንዛረብ ክንላዘብ ናይ ወትሩ መደብና ድሌትናን እዩ። እዚ መደብን ድሌትን ግን ብወገን መንግሥቲ ዝኾነ ግምት ኣይተዋህቦን። ምእንት’ዚ ሕጂ’ውን፡ ተቃውሞና ናብ ዚምልከቶ ኣካል መንግሥቲ ነቕርብ ኣሎና። ተቃውሞና ድማ ቤተክርስትያን ተልእኮኣ እትፍጸመሉ ናይ ሕክምናን ትምህርትን መጋበርታት፣ ኣብ’ዚ ቐረባ እዋናት መንግ-ሥቲ ብኢደ ወነኑ ናይ ንምውሳድ ንዝገበሮ ስጕምቲ ብዚርኢ እዩ።
2. ኣብ ከተማ ኣሥመራ ዚርከብ መድኃኔ ዓለም 2ይ ደረጃ ቤትትምህርቲ ዘርአክህነት ብትእዛዝ መንግሥቲ ካብ ዚዕጾ ደጊም ዳርጋ ክልተ ዓመቱ መሊኡ፣ እዚ ቤትትምህርቲ’ዚ ካብ 1860 ዓ.ም.ፈ. ኣትሒዙ ኣብ ዝተፈላለየ ቦታ እናተተኽለ፣ልዕሊ 100 ዓመት ዘቝጸረ፣ ማለት ኣብ ኤርትራ ዘመናዊ ትምህርቲ ቀለምን ትምህርት መንፈስን ኣላፊኑ ብምሃብ፣ ንቤተክር-ስትያንን ንሃገርን ዜገልግሉ መንእሰያት ዝዀስኰሰ ቤትትምህርቲ እዩ፣ከም’ዚ ዝበለ ርኡይኣበርክቶ ንዘለዎ ተቅዋም ምዕጻው፣ እሞ ከም ሃገርና ዝበለ ጽምኢ ትምህርቲ ኣብ ዘለዎ፣ ነዚ ውሳኔ’ዚ ምሃብ፣ ንተዓዛቢ ኾነ፡ ንሓታቲ ምላሽ ዘይተረኽበሉ ኣዝዩ ዘደንጹ ተግባር እዩ።
3. ብድሕሪኡ ድማ ሾመንተ ዚኣኽላ ብካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ዚካየዳ ማእከላት ጥዕና፣ፈጺሙ ተቐባልነት ብዘይብሉ ኣገባብ፣ ”ተደረብቲ” ብዚብል ምስምስ ናይ ምሕካም ተግባራተንከምዜቋርጻ ተገይሩ። ኣብ’ዚ ዝሓለፈ ኣዋርኅ ድማ፣ ኣስታት 21 ዚኣኽላ ናእሽቱን ዓበይትን ክሊኒካትን ናይ ጥዕና ማእከላትን ብሓይሊ ተሃጊረን፣ ንብረተንተወሲዱ። ሕጂ ኸኣ እነሆ ትማሊ ብዕለት 03.09.2019 ላዕለዋይ ደረጃ ማለት ሠለስተ ናይ ካልኣይ ደረጃ ኣብያተ ትምህርቲ፣ ሓንቲ ምስ መባእታን ማእከላይን ደረጃ እትርከበን፣
1) መባእታን ማእከላይን ላዕለዋይ 2ይን ደረጃ ቤትትምህርቲ ቅዱስ ዮሴፍ [ላ-ሳል] ከረን፣
2)ላዕለዋይ2ይ ደረጃ ቤትትምህርቲ ኣኅዋት ካፑቺኒ መንደፈራ፣
3) ማእከላይን ላዕለዋይ2ይን ደረጃ ቤትትምህርቲ ቅዱስ ፍራንቸስኮስ፣ ባጽዕ[ምጽዋዕ] ከምዚዕጸዋ ወይ ከኣ ብመንግሥቲ ከም ዚውሰዳ ተገይሩ ኣሎ። ነዚ ብዚርኢ ግቡእ ቅኑዕን ተቓውሞና ነቕርብ።
4. ኣብ ዝተፈላለየ እዋናት ከምዝተገልጸ፣ ቤተክርስትያን ዝኾነ ሓሳብ እንከተቕርብ፣ መንነታን ተልእኮኣን ብምትንታን እያ እትጅምር።ከመይ እቲ እትብሎን እትኽተሎን መትከል ነቲ ተልእኮኣን መንነታን ስዒቡ ዚመጽእ እዩ። ቤተክርስትያን ኣደን መምህርን እያ። እቲ ተኻሊኣ ኢየሱስ ክርስቶስ’ውን ከም’ቲ ንሱ ዚፍውስን ዚምህርን ዝነበረ፣ንቤተክርስትያን እውን ክትፍውስን ክትምህርን ሥልጣን ሂብዋ እዩ። ነቲ ዘለዓለማውን ኣምላኻውን ሓቂ ክትምህር’ኳ እንተኾነ ቀንዲ ስራሓ፣ ንሰብ ብመላኡ ብነፍስን ብሥጋን ኽትረድኦ ሓላፍነት ኣለዋ። በዚ መሠረትዚ ከኣ ኣብ ትምህርትን ሓፈሻዊ ምዕባሌ ወድሰብን ዓቢይ እጃም ኣለዋ። ነዚ መዝነት’ዚ እትፍጽሞ፣ኣብ ቀጽሪ ቤተክርስትያን በይኑ ብሕቱ ዘይኮነስ፣ ኣብ ኣብያተ ትምህርታ ኣብያተ ሕክምናታት፣ ኣብ’ቲ ዅሉ ንምዕባሌ ሰብ እትሰርሓሉ ማእከላትን እዩ።
5. እቲ ሓፈሻዊ ናይ ክልተ ሺሕ ዓመት ታሪኻን ጕዕዞኣን ከም ዘነጽሮ፣እዚ ዚስዕብ ካብ ባህሪኣን ተልእኮኣን ዚፍልፍል መሰልን ግዴታን ከምዘለዋ ትርዳእ። ክርስትያናዊ ትምህርቲ-እምነት ክትምህር፣ ሰብኣዊ ፍልጠትን ምዕባሌን እተካይደሉ ኣብያተ ትምህርቲ፡ ምስኡ ዚተኣሳሰር ዚንቀሳቐስን ዘይንቀሳቐስን ንብረት ክትውንን ከተካይድን መሰል ኣለዋ። እዚ መሰል’ዚ ብኣምላኽ ዝተዋህበ ባህርያዊ መሰል ስለዝኾነ፣ ብናይ ዝኾነ ይኹን ወገን ሠናይ ፍቓድን ድሌትን ዚወሃብ ወይ ዚኽላእ’ውን ኣይኮነን። እዚ ነቕ ዘይብል ሓቂ፣ ዘይትንከፍ መሰል ብዛዕባ ምዃኑ ድማ ኣብ ሕቶ ዚኣቱ ኣይኮነን።
6. ከም’ቲ ካብ ጥንቲ እሞ ኣብ መላእ ዓለም ከተዘውትሮ ዝጸንሐት፣ ዝኾነ ዓይነት ሰብኣውን መንፈሳውን ፍልጠት ዜማዕብል፣ ካብ ሙዓለ-ሕፃናት ክሳብ ደረጃ ዩኒቨርሲቲ ዜምህር በብዓይነቱ ተቅዋማት ክትውንን ከተካይድ መሰላ ግቡኣ እዩ። ከመይ መምህር እያ ተባሂሉ ኣሎ። እዚ ብቤተክርስትያን ዚካየድ ተቅዋማት እንታይ እዩ ዕላማኡ?እንተተባህለ፡-
ሀ) ናይ ሰባት ሕሊና ኰስኵስካ፣ ኣብ ኅብረተሰብን ሃገርን ምሉእን ግቡእን ቦታኦምን ኣበርክቶኦምን ዘወፍዩ ምሉኣት ሰባት ንምግባሮም፣ ፍትሕን ሰላምን መሰልን ናጽነትን ሓቅነትን ሕውነትን . . . ዚመሃሩሉ እዩ፣
ለ) ወለዲ ንውሉዶም ዚበቅዕ ትምህርቲ ኣብ ምምራጽ ዘለዎም፣ ማንም ኬሕድጎም ዘይክእል ባህርያዊ ወይ ተፈጥሮኣዊ መሰል ምእንቲ ኪኽበረሎም፣ ኣብ መዕበያ ውሉድን ብሱል ዜጋን ኣበርክቶ ንምግባር፣
ሐ) ብሥልጣኔን ብፍልጠትን ንኺዓብዩ ንዜጋታት ንምሕጋዝ፣ በቲ ዝበለጸን ብዘመናት ዝተመስከረን ናይ ቤተክር-ስትያን ሃብታም ልምድን ተመክሮ ከም ዚጥቀሙ ምግባር፣
መ) ቕኑዕን ብቑዕን ምዕባለን ወድሰብ እንተ ዘይኮይኑ፣ እዚ ናይ ቤተክርስትያን ተቅዋማት ትምህርቲ፣ ካልእ ዝኾነ ይኹን ንቡር ይኹን ስቱር መደብን ኣገባብን ከም ዘይነበሮን ከም ዘይብሉን፣ እቶም ኣብኡ ዝተማህሩን፣ ነቲ ብሉጽ ኣበርክቶኡ ዘስተማቐሩን፣ዝተፈላለየ መደብ እምነትን ሃይማኖትን፡ መሥርዕ ሕይወትን ዚኽተሉ፣ ኣብ ውሽጥን ወጻእን ሃገር ፋሕ ኢሎም ዘለዉ ሕያው ምስክር እዮም።
ማእከላት እምነትን ምዕባሌ ትምህርትን ኣብ ጕዕዞ ታሪኽ፣
7. ታሪኽ ትምህርትን ኣመዓባብላኡን ኣብ መላእ ዓለም ክንርኢ ከሎና፣ ክንክሕዶ ዘይንኽእል ሓቂ ይገሃደልና። ካብ ጥንቲ ኣትሒዙ ቀንዲ መማዕበሊ ትምህርትን ስነጽሑፍን ሥልጣኔን፣ሃይማኖታዊ ማእከላት ኮይኑ፣ ብፍላይ ኣበርክቶ ኣብያተ ክርስትያናትን መሳጊድን ኣብ ምዕባሌ ትምህርቲ ዘይነዓቕ ጥራሕ ዘይኮነስ፣ ኣዝዩ ዚድነቕን ዘንጸባርቕን ምዕራፍ ዝሓዘ እዩ።
ናብ ታሪኽ ሃገርና ንድሕሪት ምልስ ኢልና ምስ እንርኢ እውን፣ እቲ ጥንታዊ ገዳማትን ኣድባራትን ኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስትያንን፣ ጥንታዊ መሳጊድን ኣብ ጽሕፈትን ንባብን፣ ኣብ ምዕቃብ ጥንታዊ ታሪኽን ትምህርትን ዝነበሮ ጽልዋ ኣብ ቦታኡ ኮይኑ፣ ብሓፈሻኡ ኣብ ናይ’ዚ ሕዝብን ሃገርን ባህላዊ ሕንጸትን መንነትን መሠረት ዘንበረ እዩ።
8. መበቈልን ምምዕባልን ዘመናዊ ትምህርቲ ኤርትራ ኣብ ዚትንተነሉ ኵሉ፣ ካቶሊካዊ ኣብያተ ትምህርትና ብሓፈሻኡ ከኣ ኣበርክቶ ቤተክርስትያንና በዚ ዓውድ’ዚ፣ ኣንጸባራቒ ቦታ ከምዘለዎ ኵሉ ዚፈልጦ እዩ። ኣብ ኣፍሪቃ ንፈለማ ጊዜ ጥበብ ማኅተም ብምትእትታው፣ ኣብ ሃገርና ናይ ትምህርትን ጽሕፈትን ማዕጾ ዘርሓወትን ጕዕዞ ትምህርቲ ዘንሃረትን ቤተክርስትያን እያ።
ኣብ ዓዲወግሪ [ሳን ጆርጆ]፣ ኣብ ሠገነይቲ [ስኮላ ኣርተ መስቲየሪ ሳን ሚኬለ]፣ ኣብ ዓድቐይሕ፣ ኣብ ከረን[ሳልቫጎ ራጊ]፣ ኣብ ኣሥመራ [ስኮላ ቪቶሪዮ] ብጊዜ መግዛእቲ ጣልያን ንደቀባት ተደኲነን ዝነበራ፣ ብቤተክርስትያን ወይ ብናይ ቤተክርስትያን ሰባት ዚካየዳ ዝነበራ እየን። ድሕሪ ካልኣይ ኵናት ዓለም ድማ፣ ኣብ’ዛ ዘመናዊት ኤርትራ ዝቖማ፣ ካብ’ተን ኣብዛ ዋና ኸተማ ኣሥመራ ቐንዲ ቐንዲ ንምጥቃስ፣ ኮምቦኒ ኮሌጅ፣ ኣሥመራ ዩኒቨርሲቲ፣ ኮለጆ ላሳል፣ ኮለጆ ቅድስት ሓናን፣ ናይ ቀትሪ ንሕፃናት ናይ ምሸት ከኣ ንዓበይቲ ቤትትምህርቲ ቅዱስ በርናርዶስ. . . ካልኦትን ነበራ። ብፍላይ ድማኣብ ከባቢ 1965 ዓ.ም.ፈ. በዓል ሰናይ ዝኽሪ ብፁዕ ኣቡነ ኣብርሃ ፍራንስዋ ብዝወሰድዎ ተበግሶ ክሳብ 70 ዝኣኽላ ኣብያተ ትምህርቲ ኣብ ቁሸታትን ዓዳትን መላእ ኤርትራ ተጀሚረን ንነዊኅ ዓመታት ንብዙኃት ኤርትራውያን ሕጻናት ኣብ መኣዲ ትምህርቲ ከምዘሳተፋ ምዝክራ ግቡእ እዩ።
ካብ ጊዜ መግዛእቲ ጣልያን ኣትሒዙ፣ ዘመናዊ ኣመሓዳድራን ኣመሃህራን፣ ፖሊቲካዊ ጕዕዞን ስነጽሑፋዊ ምህዞን ምዕባሌ ቋንቋን ዝተኻየደ ናይ ደቂ ሃገር ፈላሚ ንጥፈታት ኵሉ፣ሳላ’ቶም ኣብ ናይ ቤተክርስትያን ተቅዋማትዝተማህሩ እዩ ተሰላሲሉ፣ ነዛ ዘመናዊት ኤርትራ ከኣ መሠረት ኣንቢሩ።ኣብ ምብግጋስ ፖሊቲካዊ መስርሕ ናይ’ዛ ሃገር፣ ኣብፖሊቲካውን ሓርነታውን ጕዕዞ ቃልሲ፣ ኣብ ኣብያተ ትምህርቲ ቤተክርስትያን ናይ ዝተማህሩ ሰባት እጃም ናቱ ዕዙዝ ምዕራፍ ዘለዎ እዩ።
9. ኣብ ታሪኽ ከም’ዚ ዝበለ ዕዙዝ ተራን እጃምን ንዘለዎ ናይ እምነት ማእከላትን ተቅዋማትን፣ ነቲ ብተግባር ዘመስከረሉን ዝተዓወተሉን መዳይ ትምህርቲ ንኸተሕድጎ፣ “ኣይምልከተካን እዩ” ምባል ደኣ ምስ ምንታይ ኪቝጸር እዩ? ተጻይ እምነትን ሃይማኖትን ብቐንዱ ክንብሎ እንተዘይኮይኑ ካልእ መግለጺ የብሉን።እምነትን ናይ ኣምላኽ ፍርሃትን ካብ ዜምህር ማእከላት ንሕፃናትን መንእሰያትን ነጺልናኸ፣ ነዛ ሃገር ከመይ ዝበለ ንኡስ ወለዶ ከነፍርየላ ተሓሲቡ ማለት እዩ?
10. ብፍላይ ናብ’ቲ ናይ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ኣብያተ ትምህርቲ ክንመጽእ ከሎና፣ ናብ’ዚ ውሳኔ’ዚ ዜብጽሕ ዝኾነ ይኹን ናይ ሥርዓተ ትምህርቲ ምዝንባል፣ ዝኾነ ይኹን ምጥሓስ ሕጊ፣ ወይ ዝኾነ ንጽፈትን ኣወሃህባ ትምህርትን ብዚርኢ፣ ኣብ ኣብያተ ትምህርትና ዝተረኽበ ካብ መሥመሩ ዝሓለፈ ወይ ዝተረፈ ኣገባብ፣ ብወገን መንግሥቲ ኣይተጠቕሰን፣ ኪጥቀስ ዚከኣል’ውን ፈጺሙ የልቦን። ኣብያተ ትምህርትና ሎሚ ጥራሕ ዘይኮነስ ካብ ቅድም ኣትሒዙ፣ ኣብ ዕለታዊ ኣሰራርሓኡን ኣብ ናይ ሃገራዊ መርመራታት ዚረአ ውጽኢት ተመሃሮኡን፣ ብብቕዓቱን ብዓይነቱን ዚልለ ብምዃኑ፣ ንኸምዚ ዝበለ መንግሥታዊ ውሳኔ ዘይኮነስ፣ ንምትብባዕን ንሽልማትን ዚዕድም ከም ዝኾነ፣ እቲ ዚምልከቶ መንግሥታዊ ኣካል ሚንስትሪ ትምህርቲ በብግዜኡ ዝቐረበሉ ጸብጻባትን ኣብ ሰነዳቱን ኣርካይቩን ሒዝዎ ዘሎ መዛግብትን ምስክሩ እዩ።
11. ብናይ ቤተክርስትያን ርድኢት፣ ብትምህርቲ ዝመጽአ መንግሥቲ ዘለዎ ግዴታን ሓላፍነትን፣ ኵሎም ዜጋታት ዜድልን ዚበቅዕን ዕድል ትምህርቲ ምርካቦም ከረጋግጽ፣ ዘለዎም መሰላትን ግዴታታትንከፍልጦም፣ሕፃናት ዚግባእ ትምህርቲ ከምዚረኽቡ ምግባር፣ ናይ ትምህርቲ ተቅዋማት፣ ብዚግባእ ዚምህሩን ዘይምህሩን፣ ነቲ ዝወጽአ ሃገራዊ መምርሕን ሥርዓተ ትምህርትን ዚኽተሉን ዘይኽተሉን፣ ምክትታል እዩ። እቲ ዚወጽእ መምርሕታት ድማነቲ ኣገባብ ኣመሃህራ ዚሕግዝ ኪኸውን፣ ንዚተባባዕ ምትብባዕ፣ ንዚሕገዝ ምሕጋዝ፣ ነቲ መኣረምታ ዜድልዮ ብምእራም፣ ብግሊ ይኹን ብናይ ኣብያተ-ክርስትያን መደባት ንዚካየድ ናይ ምምሃርን ምስትምሃርን መስርሕ ንቕድሚት ከም ዚስጕምን ምግባር እዩ።
መሰል ወለድን ቤተክርስትያንን
12. መንግሥቲ ነቲ ናይ ወለድን ናይ ቤተክርስትያንን ድሮ ውሁብን ኣድማሳውን ዝኾነ መሰል ኪፈልጥን ከኽብርን ግቡኡ እዩ። ወለዲ ንደቆም ዝደለዩዎ መደብን ኣገባብን ትምህርቲ ኪመርጹ፣ ቤተክርስትያን እውን ነቶም ኣብ ትሕቲኣ ዚርከቡ ኮነ ነቶም ኣብያተ ትምህርቲ ንዝመረጹ ወገናት ብናጽነት ክትምህር ዘለዋ መሰልን ግዴታን ኪፍለጥን ብዚግባእ ኪኸብርን ኣለዎ።
13. ካብ’ዚ ወጻኢ ምስቲ ናይ ወለድን ናይ ቤተክርስትያንን ዚጻረር ስጕምቲ ምውሳድ ግን ተቐባልነት ዘይብሉ ፍጹም ሃሳዪ እዩ። ንሕፃናት ንመንእሰያት ካብ ወለዶም፣ ካብ’ታ ብሞራልን ብሥነምግባርን እተሃንጾም ቤተክርስትያንን ቤተእምነትን ነጺልካ፣ ነዚ መሠረታዊ ባህርያውን መሰልን ግዴታን ሸለል ኢልካ ዚግበር ኣገባብ፣ “ንመንእሰያት ንምውናን” ዚግበር መደባት፣ ሲቪል ኅብረተሰብ ይኹን እቲ ናይ እምነት ማእከላት ሕግን ሥርዓትን ተኸቲሉ፣ ንወድሰብ ይጠቅም ዝበሎ ንጥፈታት ንኸየካይድ ኣብ ዚዕገተሉ ኣገባብ ኵሉ ናጽነት የልቦን፣ ኣድማሳዊ መሰል ሰብ እውን ኣይተኸብረን ማለት እዩ። ኵሉ ብመንግሥቲ ጥራሕ ከም ዚግበት ዚገብር ኣገባብ፣ናይ ውልቅን ናይ ግልን ናጽነትን ንጥፈታትን ዚዓግት እዩ፣ ናጽነትን መሰልን ኣብ ዘይተኸብረሉ፣ ሰላም ርግኣት ምዕባሌ ኪመጽእ ዘይከኣል እዩ።
ብመሠረት’ዚ መትከላት’ዚ እምበኣር፣ ነዚ በብግዜኡ ብመንጽር ተቅዋማትና ዚካየድ ዘሎ መሰል ዝጠሓሰ ውሳኔን ተግባርን ንሕና ከም መጠን ሰባት፣ ከም መጠን ኤርትራውያን ከም መጠን ካቶሊካውያን ፈጺምናኣይንቕበሎን፣ ነቲ ከም መጠን ዜጋታትን ኣመንትን ዘሎና መሰልናንግዴታናን እውን ሽለል ኣይንብሎን፣እዚ ዝተጠቕሰ መሰልና ምስ እንግፈፍ፣ ወይ ድማ ነዚ ግዴታና ምስ ዘይንፍጽም፣ እቲ ቀዳማይ ግዳይ ዚኸውን፣ እዚ ኣብዛ ሃገር ዘሎ ሰብ ወይስ ኅብረተሰብ እዩ፣ ቀጺሉ ድማ ሃገር ብዓባያ እያ። በቲ ዝቖመሉ ዕላማኡን፣ በቲ ብተግባር ዝተራእየ ኣሰራርሓኡን፣ ተቅዋማትና ብምሉኡ ንረብሓ ሕዝብን ሃገርን ምዃኑ ስለ ንተኣማመን፣ እዚ ተቅዋማት’ዚ ኪህገርን መሰል ቤተክርስትያን ኪድፈርን ከሎ ጕድኣቱ ንመላእ ሕዝብን ሃገርን ምዃኑ ኪፍለጥ ኣለዎ።
መዛዘሚ
14. ኣብ’ዚ ሃገር’ዚ ንዘሎን ኵነትን ንዝሓለፈ ታሪኽን ድሕሪ ፈቲሽና፣ ብፍላይ ብመንጽር ትምህርቲ እቲ ናይ ቤተክርስትያን ታሪኽ ዘንጸባርቅ ደኣ’ምበር ዝኮነ ይኹን ጸሊም ነጥቢ ከም ዘይርከቦ ኣፍና መሊእና ክንዛረበሉ እንኽእል እዩ። ምእንት’ዚ እዚ ሕጂ፦
ሀ) ብመንጽር ናይ ትምህርትን ሕክምናን ተቅዋማትና ዚወሃብ ዘሎ ውሳኔታትን፣ ስዒቡ ዚካየድ ዘሎ ተግባራትን፣ ንናይቤተክርስትያን መሰልን ናጽነት እምነትን ብቐንዱ ዚጻባእ ተግባር፣ ኣብ’ቲ መደብ እምነታን መንነታን ኣገልግሎታን ብቐንዱ ዚኣቱ፡ ስለዚ ኸኣ ንህላዌኣ ዚትንክፍ ምዃኑ እናገለጽና፣እዚ ኣገባብ’ዚ ዳግመ ግምት ተገቢሩሉ ብዝቐልጠፈ ደው ኪብል ነሓትት፣
ሁ) ተቅዋማት ቤተክርስትያን ኵሉ ከም መጠን ናይ ደቂ ኤርትራ ተቅዋማት፣ ነቲ ሥሩዕን ብሉጽን ትምህርታውን ሕክምናውን ኣገልግሎቱ ብናጽነትን ብተወፋይነትን ንኺቕጽል ዕድል ኪወሃብ ነሓትት፣
ሂ) ዝኾነ ይኹን ኪእረም ወይ ኪዕረ ዚድለ እንተሎ ድማ፣ ብሓባራዊ ዘተን ምርድዳእን ኪፍታሕ ጽቡቕ ጥራሕ ዘይኮነ እቲ ኡንኮ መንገዲ ምዃኑ ነመልክት።
15. ቤተክርስትያን እምበኣር በቲ ብዘመናት ዘጥረየቶ ተመክሮን ነዊሕ ትውፊትን በቲ ዘለዋ ዓቕምን፣ ኣብ ምዕባሌ ሰባት ቀንዲ ረቛሒ ብዝኾነ ዓውዲ ትምህርቲ፣ ነቲ መንግሥታዊ መምርሒ ትምህርቲ ብምሕላው፣ በብዓይነቱ ኣብያተ ትምህርቲ ከተካይድ፣ መደባ ምዃኑ ትገልጽ። ነዚ መደባ ዚቃወም ዝኾነ ዓይነት ውሳኔ ወይ ኣገባብ ነቲ ናጽነታን መሰላታን ከም ዝገፈፋ ትርዳእ፣ እዚ መሰላት’ዚ ዳግም ክሳብ እትለብስን ናጽነታ ክሳብ እትጭብጥን ከኣ ምስ ምእመናና ኮይና ናብ ኣምላኽ ዘየቋርጽ ጸሎትን ስእለትን ተብጽሕ፣ ብሕጋዊ መንገዲ ከኣ ናብ ዚምልከቶ ኣካል ምእንቲ መሰላ ኣቤት!! ካብ ምባል ዓዲ ኣይትውዕልን።
ኣምላኽ ንሃገርና፣ ሃገር ሰላምን ፍትሕን ሃገር ርትዕን ፍቕርን ይግበረልና።
ካቶሊካውያን ጳጳሳት
1. ኣቡነ መንግሥተኣብ ተስፋማርያም ፣ ሊቀጳጳስ ዘመንበረ ኣሥመራ
2. ኣቡነ ቶማስ ዖስማን፣ ጳጳስ ዘመንበረ ባረንቱ
3. ኣቡነ ኪዳነ የዕብዮ፣ ጳጳስ ዘመንበረ ከረን
4. ኣቡነ ፍቅረማርያም ሓጎስ፣ ጳጳስ ዘመንበረ ሠገነይቲ
ቅዳሕ ናብ፦
1. ሚንስትሪ ዞባዊ ምምሕዳር
2. ቤት ጽሕፈት ሃይማኖታዊ ጕዳያት
3. ቤትጽሕፈት ህ.ግ.ደ.ፍ.
4. ምምሕዳር ዞባ ደቡብ
5. ምምሕዳር ዞባ ዓንሰባ
6. ምምሕዳር ዞባ ሰሜናዊ ቐይሕ ባሕሪ
Re: ምሉእ ትሕዝቶ መልእኽቲ ጳጳሳት ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ኤርትራ ንሚኒስተር ትምህርቲ ኣቶ ሰመረ ርእሶም (ምኒስተር ትምህርቲ ኤርትራ)
ስልጡን በሆነ መንገድ ኤርትራዉያን የካቶሊክ ቤተክርስትያን ጳጳሶች ለሚመለከታቸው የመንግሥት አካላት ያሰራጩት ግልጽ መልእክትን፣ ኢትዮጵያዉያን ወንድሞቻችን በተለይም ወጣቱ ስልጡን ጠቅላዪ ሚኒስትራቸው ዶ/ር ኣብዪ ኣሕመድ ይማሩበት እንዲሁም የኤርትራዉያን ካቶሊክ ጳጳሳትን ስልጡን አካሄድ ይገነዘቡበት ዘንድ እናጋራቸዋለን። የኤርትራ ትምህርት ሚንስተር ለዚህ ስልጡንና አግባብነት ላለው ግልጽ ጥያቄና ስሞታ እስካሁኗ ደቂቃ ድረስ አንዳችም ምላሽ አለመስጠቱ ይታወቃል። የኤርትራ መንግሥት “ናትና ኣይንህብን ዘይናትና ኣይንደልን” ማለትም “የራሳችንን አንሰጥም የሰውንም አንሻም” በሚል መፈክሩ የታወቀ ቢሆንም ቅሉ፣ ያለ አንዳች ውይይት እየወረሳቸው ያሉትን እነዚህን ዓመታት ያስቆጠሩ የትምህርትና የጤና ተቋሞች ገንብታና አንጻ ለአገልግሎት ያበቃቻቸው የባለቤትነትም ህጋዊ መብትና ህጋዊ ማረጋገጫን የያዘችው የኤርትራ ካቶሊካዊት ቤተክርስትያን መሆኗ ይታወቃል። ፍትሐዊዉንና ስልጡኑን የኤርትራ ካቶሊካዉያን ጳጳሳት አካሄድ ለማጤን ይቻል ዘንድ የጳጳሳቱ መልእክት ሙሉ ይዘትን በአፍሪካ ቀንድ ቋንቋዎች በአንዱና በዋንኛዉ እንደሚከተለው ለኢትዮጵያዉያን ወንድሞቻችን ስናጋራቸው በዚህ ግሩም ድረ-ገጽ ታሪኩን ለመጪዉ ትውልድ እየከተብን እንዲሁም “የሰው ገንዘብ አትመኝ” የሚለውንም ትእዛዝ ማክበር እንደሚገባ ለመንግስታትም ጭምር በማሳሰብ ነው። መልካም ንባብ!
ሃገረ ኤርትራ - ለ አቶ ሰመረ ርእሶም - ትምህርት ሚንስተር - ኣሥመራ።
ኣሥመራ 04.09.2019 (፳፱ ነሐሴ ፳፻፲፩ ዓ. ም. )
ጕዳዩ፦ በመንግሥት ስለተወሰዱት (የተወረሱ) የቤተክርስትያን ትምህርት ቤቶች
1. እኛ የካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ጳጳሶች፣ ሃገራችንን ሆነ የሃገራችን ካቶሊካዊት ቤተክርስትያንን በሚመለከት ጉዳይ፣ ከመንግሥት አካላት ጋር ተገናኝተን ለመነጋገርና ለመወያየት ሁሌም ፍላጎታችንና መሻታችን ነው። ይህ ፍላጎታችን ግን በመንግሥት በኩል ምንም ዓይነት ትኵረት አልተሰጠውም። ስለሆነም አሁንም፣ ተቃውሟችንን ለሚመለከተው የመንግሥት አካል አቅርበናል። ተቃውሟችንም ቤተክርስትያን ተልእኾዋን የምትፈጽምበት የህክምናና የትምህርት ተቋማት ክንፎቿን፣ ከቅርብ ግዜ ጀምሮ መንግሥት በማን አለብኝነት ለመውሰድ የሚያደርገውን እርምጃ በተመለከተ ነው።
2. በአሥመራ ከተማ ውስጥ የሚገኝ የመድኃኔ ዓለም 2ይ ደረጃ የዘርአክህነት ትምህርት ቤት በመንግሥት ትእዛዝ መሰረት ከተዘጋ ሁለት አመቱ ተቃርቧል፣ ይህ ትምህርት ቤት ከ1860 እ.ኤ.አ ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎች እየተተከለ፣ ከ100 ዓመት በላይ ያስቆጠረ፣ ይህም ማለት በኤርትራ ውስጥ ዘመናዊ ትምህርትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጋራ ወይም በጥምረት በመመገብ፣ ቤተክርስትያንና ሃገርን የሚያገለግሉ ወጣቶችን የመለመለ ትምህርት ቤት ነው፣ ይህን የመሰለ ግልጽና ልዑል አበርክቶ ያለውን ተቋም መዝጋት፣ በዚች የትምህርት ጥማት ባለባት ሃገራችን ይህን ውሳኔ ማሳለፍ፣ ለታዛቢም ሆነ፣ ለጠያቂ ምንም ዓይነት ምላሽ የማይገኝለት እጅግ የሚገርም ይህ ነው ሊባል የማይችል ተግባር ነው።
3. በመቀጠልም ስምንት የሚሆኑ በካቶሊካዊት ቤተክርስትያን የሚተዳደሩ የጤና ተቋማትን፣ በምንም ዓይነት መለኪያ ተቀባይነት በሌለው አኳኋን፣ “ተደራቢዎች” በሚል አጉል ፈሊጥ የህክምና ተግባራቸውን እንዲያቋርጡ ተደርጓል። ባለፉት ወራትም፣ 21 የሚሆኑ ትንንሽና ትልልቅ ክሊኒኮችና የጤና ተቋማት በሃይል ተወርሰዋል፣ ንብረታቸውም ተወስዷል። አሁን ደግሞ ትላንት በ03.09.2019 እ.ኤ.አ. የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ማለትም ሦስት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ከነዚህም አንዷ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚገኝባት ትምህርት ቤቶች፦
1) የቅዱስ ዮሴፍ [ላ-ሳል] ከረን አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
2) የካፑቺኒ ወንድሞች ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመንደፈራ
3) የቅዱስ ፍራንቸስኮስ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃና ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በምጽዋ
እንዲዘጉ ወይም በመንግሥት እንዲወሰዱ (እንዲወረሱ) ተደርጓል። ይህን በተመለከተም ተገቢውንና ቀጥተኛውን ተቃውሟችንን እናቀርባለን።
4. በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደተገለጸው፣ ቤተክርስትያን የተለያየ ሓሳቦቿን ስታቀርብ የምትጀምረው፣ ማንነቷንና ተልዕኾዋን በመተንተን ነው። ይህም የምትሰብከውንና የምታስተምረውን ዓላማዋ ማንነቷንና ተልዕኮዋን ተከትሎ የሚመጣ ነው። ቤተክርስትያን እናትም መምህርም ነች። መስራቿ ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስና ያስተምር እንደነበረው ሁሉ፡ ለቤተክርስትያንም እንድትፈውስና እንድታስተምር ሥልጣንን ሰጥቷታል። ዋንኛ ስራዋ አምላካዊዉንና ዘላለማዊዉን ሓቅ ማስተማርና መስበክ ቢሆንም እንኳ፡ የሰው ልጅን በነፍስና በሥጋ የመርዳት ሃላፊነትም አለባት። ይህን ሃላፊነቷንም በተግባር የምትፈጽመው፡ በቤተክርስትያን አጥር ግቢ ውስጥ ብቻ ታጥራ ሳይሆን፣ በትምህርት ቤቶቿና የሕክምና ተቋሞቿ እንዲሁም ባጠቃላይ ለሰው ልጅ ሁለንተናዊ እድገት በምትሰራባቸው ማእከላቶቿ አማካኝነት ነው።
5. አጠቃላይ የሁለት ሺ ዓመት ታሪኳና ጉዞዋ በግልጽ እንደሚያሳየው፣ ይህ ተግባሯ ከባህሪዋና ከተልእኾዋ አኳያ የሚመነጭ መብትና ግዴታ እንዳላት ጠንቅቃ ትረዳለች። ክርስትያናዊ የእምነት ትምህርትን ስታስተምር፡ ሰብአዊ እውቀትንና እድገትን የምታስተምርበትና የምታካሂድበት ትምህርት ቤት፣ ከዚህ ጋር የሚያያዝ ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ንብረትን የማፍራትና የማካሄድ መብት አላት። ይህ መብትም በአምላክ የሚሰጥ ባህርያዊ መብት ስለሆነ፣ በማንኛውም አካል በጎ ፍቃድ ወይ ፍላጎት የሚቸር ወይ የሚሰጥ ወይም የሚከለከል አይደለም። ይህ የጸና እውነታም፣ በምንም መልኩ የማይደፈር መብት ስለመሆኑ አያጠያይቅም።
6. ከጥንት ከጥዋቱ በመላው ዓለም እያዘወተረችው ያለው፣ ማንኛውንም ሰብአዊና መንፈሳዊ ዕውቀትን የሚያሳድግና የሚያበለጽግ፣ ከሙዓለ-ሕፃናት እስከ የዩኒቨርስቲ ደረጃ ድረስ የሚያስተምሩ የተለያዩ ተቋማትን መመስረትና ማካሄድ መብቷና ግዴታዋ ነው። ለምን ቢባል መምህር ናትና ነው። እነኝህ በቤተክርስትያን የሚካሄዱ ተቋማት ዓላማቸው ምንድን ነው? ከተባለ፦
ሀ) የሰው ልጆችን ኅሊና በመኮትኮትና በመመልመል ፣ በኅብረተሰብና በሀገር ውስጥ በብቃትና በተገቢ ሁኔታ አስፈላጊውን ገንቢ ሚና የሚያበረክቱ ብቁ ዜጎች ይሆኑ ዘንድ፣ ስለ ፍትሕ ሰላም መብትና ነጻነት ሓቀኝነትና ወንድማማችነት . . . የሚማሩበት ነው፣
ለ) ወላጆች ለልጆቻቸው ብቁ የሆነ ትምህርትን የመምረጥ ያላቸውን ማንም ሊገፍፋቸውና ሊቀማቸው የማይችልን ባህርያዊና ተፈጥሯዊ መብት ይከበርላቸው ዘንድ፣ ትውልድን በማነጽና የበሰለ ዜጋን በማፍራት ረገድ የበኩሏን አስተዋጻኦ ለማድረግ፣
ሐ) ዜጎች በሥልጣኔና በዕውቀት እንዲያድጉ ለማገዝ፣ በበለጠውና የዘመናት ልምድ ማካበቱ በተመሰከረለት የቤተክርስትያን ሃብታም ልምድና ተሞክሮ እንዲጠቀሙ ለማድረግና ለማስቻል፣
መ) ቅኑና ብቁ የሆነ ለሰው ልጆች እድገት ከመትጋት ውጭ፣ እኒህ የቤተክርስትያን የትምህርት ተቋሞች፣ ሌላ ከዚህ ውጭ የሆነ ድብቅ አላማ ሆነ አካሄድ እንዳልነበራቸው እንደሌላቸውም፣ በትምህርት ተቋማቱ ውስጥ ተምረው፣ ብርቅና ድንቅ ይዞታዉን ያጣጣሙ፣ የተለያዩ የእምነትና የሃይማኖት እንዲሁም የህይወት ዘይቤዎችን የሚከተሉ፣ በሃገር ውስጥና በሃገር ውጭ በተለያዩ ሃገራት ተዘርግተው የሚገኙት ዜጎች ህያው ምስክሮች ናቸው።
የእምነት ማእከላትና የትምህርት እድገት በታሪኽ አዃያ
7. የትምህርት ታሪኽንና አመጣጡን እንዲሁም አስተዳደጉን በመላው ዓለም ስናጤንና ስናጠና፣ አንድ በፍጹም ልንክደው የማንችል ሓቅ ቁልጭ ብሎ ይታያል። ከጥንት ከጥዋቱ የትምህርትና የሥነጽሑፍ መኮትኮቻና ማሳደጊያ ቦታዎች የሃይማኖት ተቋሞች ሲሆኑ፣ በተለይም ቤተክርስትያንና መስጊዶች ለትምህርት እድገት የነበራቸው አስተዋጽኦና ገንቢ ሚና በቀላል የሚገመት ብቻ ሳይሆን እጅግ አስደናቂና አንጸባራቂ ምዕራፍን የያዘ ነው።
የሃገራችንን ታሪክ ወደኋላ ተመልሰን ስንመለከትም፣ የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጥንታዊ ገዳሞችና ደብሮች፣ እንዲሁም ጥንታዊ መስጊዶች፡ ከጽሑፍና ከንባብ አኳያ፡ ጥንታዊ ታሪኽንና ትምህርትን በማቀብ ረገድ የነበራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፣ ባጭር አገላለጽ የዚህ ህዝብንና ሃገርን ባህላዊ ሕንጸትንና ለማንነቱና ለምንነቱም መሰረትን ያስቀመጠ ገንቢ ሚና ተጫውተዋል።
8. የኤርትራ ዘመናዊ ትምህርት ውልደትና እድገት በሚገለጽበትና በሚተነተንበት ወቅትም፣ ካቶሊካዊ ትምህርት ቤቶቻችን እንዲሁም ቤተክርስትያናችን ባጠቃላይ በዚህ ረገድ፣ እጅግ ደማቅና አንጸባራቂ ቦታ እንዳላት ማንም ሰው የሚያዉቀው ፍንትዉ ብሎ የሚታይ ሓቅ ነው። በአፍሪካ ምድር ለመጀመርያ ግዜ የኅትመት ጥበብን በማስተዋወቅ፣ በሃገራችን የትምህርትና የጽሕፈትን በር የከፈተችና የትምህርትን ጉዞ ያፋጠነች ቤተክርስትያን ነች።
በዓዲወግሪ [ሳን ጆርጆ]፣ በሠገነይቲ [ስኮላ ኣርተ መስቲየሪ ሳን ሚኬለ]፣ በዓድቐይሕ፣ በከረን[ሳልቫጎ ራጊ]፣ በኣሥመራ [ስኮላ ቪቶሪዮ] በጣልያን ግዛት ዘመን ለሃገራችን ሰዎች መማርያ የተመሰረቱ ትምህርት ቤቶች ነበሩ፣ እነኝህም በቤተክርስትያን ወይም በቤተክርስትያን ሰዎች የሚተዳደሩና የሚካሄዱ የነበሩ ናቸው። ከሁለተኛ የዓለም ጦርነት በኋላም በዝች በዘመናዊቷ ኤርትራ የተመሰረቱት በተለይም በርእሰ ከተማችን በአሥመራ የተመሰረቱትና የተቋቋሙት የትምህርት ማእከላት ለአብነት ለመጥቀስ፦ ኮምቦኒ ኮሌጅ፣ አሥመራ ዩኒቨርስቲ፣ ኮለጆ ላሳል፣ ኮለጆ ቅድስት ሓናና፣ በቀትር ህጻናትን በምሽት ደግሞ ጎልማሶችን የሚያስተምረው የቅዱስ በርናርዶስ ትምህርት ቤትና . . . ሌሎችም ነበሩ። በተለይም በ 1965ዓ.ም (እ.ኤ.ኣ) ለትምህርት ልዩ ፍቅር በነበራቸው በተወዳጁ ብፁዕ አቡነ ኣብርሃ ፍራንስዋ አነሳሽነት እስከ 70 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ ቀየዎች በመላዉ ኤርትራ ተመስርተውና ለረዢም ዓመታት ብዙ ኤርትራዉያን ሕፃናትን በትምህርት ገበታ እንዲሳተፉ አስችለው እንደነበር ማስታወስ ተገቢ።
ከጣሊያን የአገዛዝ ዘመን ጀምሮ፣ ዘመናዊ አስተዳደርንና የአማማር ዘዴንና ዘይቤን፣ ፖለቲካዊ ጉዞንና ስነጽሑፋዊ ፈጠራን እንዲሁም የቋንቋን ዕድገት በተመለከተ ረገድ የተካሄደን የህዝባችን የመጀመርያ ተግባራቶች በብዛት በስኬት የተካሄዱት፣ በቤተክርስትያን ተቋሞች በተማሩ ልጆቻችን ብርታት ነው። ይህም ለዘመናዊቷ ኤርትራ መሰረት ሆኗል። በዝች ሃገራችን የፖለቲካ ሂደት ጅማሬም ሆነ በፖለቲካዊና በነጻነት የትግል ጉዞ ሂደትም፣ በቤተክርስትያን ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተማሩ ሰዎች ሚና የራሱን ትልቅ ምዕራፍ የያዘ ነው።
9. በታሪኽ ይህን የመሰለ ትልቅ ሚናና ምእራፍ ያበረከቱትን የእምነት ተቋሞችና ማእከሎች፣ በተግባር በትምህርቱ ዘርፍ ያስመዘገቡትን ድልና ስኬት መቀማትና መካድ፣ የትምህርቱ ዘርፍን “ኣይመለከታችሁም” ብሎ ማለት ታድያ ከምን ይቆጠራል? ይህን አካሄድ ከእምነትና ከሃይማኖት ጋር መጻረር ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት መግለጫ ሊገኝለት አይችልም። እምነትንና ፈሪሃ እግዚአብሄርን ከሚያስተምሩ ማእከላት ሕፃናትንና ወጣቶችን ነጥለንስ፣ ለዝች ሃገር ምን ዓይነት አዲስ ትውልድ እንድናፈራላት ነው የታሰበው ማለት ነው?
10. በተለይም የካቶሊክ ቤተክርስትያን ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ፡ ይህን መሰሉን ውሳኔ ለመወሰን የሚያስገድድ አንዳችም ዓይነት የትምህርት ሥርዓትን የማዛባት፣ ወይም ሕግን የመጣስ፣ ማለትም የትምህርት ጥራትንና ብቃትን እንዲሁም አማማርን ማለትም የመማር ማስተማር ሂደትን በተመለከተ፣ በትምህርት ቤቶቻችን የተገኘ እክል ወይም ከተገቢው መሥመር የማፈንገጥ አዝማሚያ፣ በመንግሥት በኩል እንደ ማስረጃነት አልተጠቀሰብንም። ሊጠቀስ የሚችል እክል ወይ ጉድለትም በጭራሽ የለንም። ትምህርት ቤቶቻችን ዛሬ ብቻ ሳይሆን ከምስረታቸው ጀምሮ፣ በዕለታዊ አሰራራቸውና እንዲሁም ተማሪዎቻቸው በሃገራዊ ፈተናዎች የሚያስመዘግቡት ድንቅ ውጤት፣ በብቃታቸው ሆነ በዓይነታቸው የተመሰገኑና የተመሰከረላቸው በመሆናቸው፣ ይህን ለመሰለው አሉታዊ የመንግስት ውሳኔ ሳይሆን፣ ሽልማትና ማበረታታት ሊቸራቸው የሚገባ መሆኑን፣ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ማለትም የትምህርት ሚኒስቴር በየግዜው የሚቀርቡለትን ሪፖርትና በአርካይቮቹ ይዟቸው የሚገኙት መዛግብቶቹ ምስክር ናቸው።
11. እንደ የቤተክርስትያናችን ግንዛቤ፡ ትምህርትን በተመለከተ፡ የመንግሥት ግዴታና ኃላፊነት፡ ዜጎች ሁሉ አስፈላጊዉንና ብቁ የሆነን የትምህርት ዕድል ማግኘታቸውን ማረጋገጥ፣ መብትና ግዴታቸውንም መግለጽ፣ ሕፃናት ተገቢዉን ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ፣ የትምህርት ተቋሞች በተገቢው ሁኔታ እያስተማሩ ናቸው ወይስ አይደሉም ብሎ መቆጣጠር፡ በሃገር ደረጃ የሚወጡ መመሪያዎችንና የትምህርት ሥርዓትን እየተከተሉ ናቸው ወይስ አይደሉም ብሎ መቆጣጠር ነው። የሚወጣው የትምህርት መመሪያም የመማርና ማስተማሩን ሂደት የሚያግዝ ይሆን ዘንድ፣ መበረታታት የሚገባዉን አካል ማበረታታት፣ ሊታረም የሚገባዉን አካልም በማረም፣ በግል ይሁን በቤተክርስትያን አማካኝነት የሚካሄድን የመማርና የማስተማር ሂደት ወደ ፊት ይበልጥ ይራመድ ዘንድ ማስቻል ነው።
የቤተክርስትያንና የወላጆች መብት
12. መንግሥት በዓለምአቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለዉን የወላጆችንና የቤተክርስትያንን መብት ማወቅና ማክበር ግዴታው ነው። ወላጆች ለልጆቻቸው ያሻቸውን የትምህርት ዓይነትና የአማማር ዘዴን የመምረጥ፣ ቤተክርስትያንም በውስጧ ያሉ ልጆቿን ሆነ ትምህርት ቤቶቿን መርጠው የሚመጡ ማናቸውም ዜጎችን በነጻነት የማስተማር መብቷና ግዴታዋ በአግባቡ ሊታወቅና ሊከበር ይገባል።
13. ከዚህ ባሻገር የወላጆችንና የቤተክርስትያንን መብት በሚጻረር መልኩ እርምጃዎችን መውሰድ ተቀባይነት የሌለውና እጅጉኑ ጎጂ አካሄድ ነው። ሕፃናትንና ወጣቶችን ከወላጆቻቸው፣ በሞራልና በሥነምግባር ከምታንጻቸው ቤተክርስትያንና የእምነት ቤታቸው በመነጠል፣ ይህን መሠረታዊና ባህርያዊ መብትንና ግዴታን ችላ በማለት የሚኬደው፣ “ወጣቶችን ለመያዝ” የሚደረግ አካሄድ፤ ሲቪል ኅብረተሰብ ሆነ የእምነት ማእከላት ሕግና ሥርዓትን ተከትለው፣ ለሰው ልጆች ይጠቅማል ብለው ያሰቡበትን አሰራራቸውን እንዳይተገብሩ የሚገታበት አካሄድ ሁሉ ነጻነት የለበትም፤ በዚህ ሁኔታ ዓለም አቐፋዊ የሰው ልጆች መብትም አልተከበረም ማለት ነው። ማንኛውም ስራ በመንግስት አካል ብቻ የሚያዝበት አሰራርና አካሄድ፣ የግልንና የሰብአዊ ነጻነትንና አካሄድን የሚገታ አካሄድ ነው፣ ነጻነትና መብት ባልተከበረበት ደግሞ፣ ሰላም ሆነ መረጋጋት እንዲሁም እድገት ሊመጣና ሊገኝ አይችልም።
እንግዲያዉኑስ በዚህ መርህ መሠረት፣ በየጊዜው ከተቋሞቻችን አንጻር የሚደረገው መብትን የመጋፋት የመርገጥና የመጣስን ውሳኔና ተግባር እኛ እንደግለሰቦች፣ እንደ ኤርትራዉያን ዜጎችና እንደ ካቶሊካዉያን መጠን በጭራሽ አንቀበለዉም፤ ዜጎችና አማንያን እንደመሆናችን መጠን ያለንን መብትና ግዴታም ችላ አንለዉም፣ ይህ እላይ የጠቀስነውን መብታችንን ስንገፈፍ ወይም የጠቀስናቸውን ግዴታዎቻችንን ሳንወጣ ስንቀር፣ በዋነኛነት የሚጎዳው በዚች ሃገራችን ውስጥ ያለው ዜጋ ወይ ኅብረተሰብ ነው፣ ቀጥሎም ሃገር እንደ ሃገርነቷም ትጎዳለች። በተቋቋሙበት ዓላማና በተግባር በተፈተኑበት አሰራራቸው መሰረት፣ ተቋሞቻችንን በሙሉ ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መሆኑን ስለምንተማመንባቸው፤ እነዚህ ተቋሞች ሲወረሱና የቤተክርስትያን መብት ሲደፈር በዋነኛነት የሚጎዳው ሕዝብና ሃገር መሆኑን መረዳትና መታወቅ አለበት።
መደምደሚያ
14. በዚህች አገራችን ውስጥ አሁን ያለንበትን ሁኔታና ያለፈውን ታሪኽ በጥልቀት ከመረመርን በኋላ፣ በተለይም በትምህርት ረገድ የቤተክርስትያን ታሪኽ አንጸባራቂ መሆኑን እንጂ አንዲትም ጥቁር ነጥብ ወይም ጉድፍ እንደማይገኝበት አፋችንን ሞልተን መናገር እንችላለን። ስለሆነም በአሁኑ ወቅት፦
ሀ) ከትምህርትና የሕክምና ተቋሞቻችን አንጻር የሚተላለፈው ውሳኔና፣ ውሳኔውን ተከትሎ የሚካሄደው ተግባር፣ በዋነኛነት የቤተክርስትያንን መብትና የእምነት ነጻነት የሚጻረር ተግባር፣ በእምነቷ በማንነቷና በአገልግሎቷ ውስጥ ጣልቃ ገብነትና ህልውናዋን የሚፈታተን መሆኑን እየገለጽን፡ ይህ ተግባር ዳግም ተመርምሮ በአፋጣኝ እንዲቆም እንጠይቃለን፣
ሁ) የቤተክርስትያን ተቋማት የኤርትራ ልጆች ተቋም እንደመሆኑ መጠን፣ መደበኛውንና ድንቁን የትምህርትና የሕክምና አገልግሎቱን በነጻነትና በታታሪነትን ይቀጥል ዘንድ ዕድል እንዲሰጠው እንጠይቃለን፣
ሂ) ሊታረም ወይ ሊወገድ የሚገባው ማንኛውም እንከን ካለም፣ በጋራ ውይይትና የመግባባት መንፈስ እንዲፈታ ማድረግ መልካም ብቻ ሳይሆን ብቸኛው መንገድ መሆኑን እናስገነዝባለን።
15. እንግዲያዉኑስ ቤተክርስትያን ለዘመናት ባካበተችው ልምድ፣ ረዢም ትዉፊትና ዓቅም ኣኳያ፣ ለሰው ልጆች እድገት ወሳኝ ሚና ባለው በትምህርቱ ዘርፍ፣ የመንግስትን መመሪያ በመከተል፡ የተለያዩ ትምህርት ቤቶችን መክፈትና ማካሄድ፣ ከተልእኾዋ አንዱ ክፍል መሆኑን መግለጽ ትወዳለች። ይህን ተልእኮዋን የሚቃወም ማንኛውም ዓይነት ውሳኔ ወይ ሂደት ነጻነቷንና መብቷን እንደገፈፋት ትረዳለች፣ ይህን መብቷን ዳግም እስክትጎናጸፍና ነጻነቷን እስክትጨብጥ ድረስ ከመእምናኖቿ ጋር ሆና ወደ አምላክ ያለማቋረጥ ጸሎቷንና ምህለላዋን ታሳርጋለች፣ በህጋዊ መንገድም ለሚመለከተው አካል መብቷ ይከበር ዘንድ ስሞታዋን እያቀረበች “ጥያቄዋ ይመለስ መብቷም ይከበር ዘንድ አቤቱታዋን ሳታሰልስ ከማቅረብ አትቦዝንም።
አምላክ ሃገራችንን፣ የሰላምና የፍትህ ሃገር የርትዕና የፍቅር ሃገር ያድርግልን።
ካቶሊካውያን ጳጳሶች
1. ኣቡነ መንግሥተኣብ ተስፋማርያም ፣ ሊቀጳጳስ ዘመንበረ ኣሥመራ
2. ኣቡነ ቶማስ ዖስማን፣ ጳጳስ ዘመንበረ ባረንቱ
3. ኣቡነ ኪዳነ የዕብዮ፣ ጳጳስ ዘመንበረ ከረን
4. ኣቡነ ፍቅረማርያም ሓጎስ፣ ጳጳስ ዘመንበረ ሠገነይቲ
ኮፒ ለ፦
1. ዞባዎች አስተዳደ ሚንስትሪ
2. ሃይማኖታዊ ጕዳዮች ጽሕፈት ቤት
3. ህ.ግ.ደ.ፍ. ጽሕፈት ቤት
4. ደቡብ ዞባ አስተዳደር
5. ዓንሰባ ዞባ አስተዳደር
6. ሰሜናዊ ቀይ ባሕር ዞባ አስተዳደር
https://www.vaticannews.va/ti/church/ne ... zione.html
ሃገረ ኤርትራ - ለ አቶ ሰመረ ርእሶም - ትምህርት ሚንስተር - ኣሥመራ።
ኣሥመራ 04.09.2019 (፳፱ ነሐሴ ፳፻፲፩ ዓ. ም. )
ጕዳዩ፦ በመንግሥት ስለተወሰዱት (የተወረሱ) የቤተክርስትያን ትምህርት ቤቶች
1. እኛ የካቶሊካዊት ቤተክርስትያን ጳጳሶች፣ ሃገራችንን ሆነ የሃገራችን ካቶሊካዊት ቤተክርስትያንን በሚመለከት ጉዳይ፣ ከመንግሥት አካላት ጋር ተገናኝተን ለመነጋገርና ለመወያየት ሁሌም ፍላጎታችንና መሻታችን ነው። ይህ ፍላጎታችን ግን በመንግሥት በኩል ምንም ዓይነት ትኵረት አልተሰጠውም። ስለሆነም አሁንም፣ ተቃውሟችንን ለሚመለከተው የመንግሥት አካል አቅርበናል። ተቃውሟችንም ቤተክርስትያን ተልእኾዋን የምትፈጽምበት የህክምናና የትምህርት ተቋማት ክንፎቿን፣ ከቅርብ ግዜ ጀምሮ መንግሥት በማን አለብኝነት ለመውሰድ የሚያደርገውን እርምጃ በተመለከተ ነው።
2. በአሥመራ ከተማ ውስጥ የሚገኝ የመድኃኔ ዓለም 2ይ ደረጃ የዘርአክህነት ትምህርት ቤት በመንግሥት ትእዛዝ መሰረት ከተዘጋ ሁለት አመቱ ተቃርቧል፣ ይህ ትምህርት ቤት ከ1860 እ.ኤ.አ ጀምሮ በተለያዩ ቦታዎች እየተተከለ፣ ከ100 ዓመት በላይ ያስቆጠረ፣ ይህም ማለት በኤርትራ ውስጥ ዘመናዊ ትምህርትንና መንፈሳዊ ትምህርትን በጋራ ወይም በጥምረት በመመገብ፣ ቤተክርስትያንና ሃገርን የሚያገለግሉ ወጣቶችን የመለመለ ትምህርት ቤት ነው፣ ይህን የመሰለ ግልጽና ልዑል አበርክቶ ያለውን ተቋም መዝጋት፣ በዚች የትምህርት ጥማት ባለባት ሃገራችን ይህን ውሳኔ ማሳለፍ፣ ለታዛቢም ሆነ፣ ለጠያቂ ምንም ዓይነት ምላሽ የማይገኝለት እጅግ የሚገርም ይህ ነው ሊባል የማይችል ተግባር ነው።
3. በመቀጠልም ስምንት የሚሆኑ በካቶሊካዊት ቤተክርስትያን የሚተዳደሩ የጤና ተቋማትን፣ በምንም ዓይነት መለኪያ ተቀባይነት በሌለው አኳኋን፣ “ተደራቢዎች” በሚል አጉል ፈሊጥ የህክምና ተግባራቸውን እንዲያቋርጡ ተደርጓል። ባለፉት ወራትም፣ 21 የሚሆኑ ትንንሽና ትልልቅ ክሊኒኮችና የጤና ተቋማት በሃይል ተወርሰዋል፣ ንብረታቸውም ተወስዷል። አሁን ደግሞ ትላንት በ03.09.2019 እ.ኤ.አ. የከፍተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ማለትም ሦስት የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶችና ከነዚህም አንዷ አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የሚገኝባት ትምህርት ቤቶች፦
1) የቅዱስ ዮሴፍ [ላ-ሳል] ከረን አንደኛና መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃ እንዲሁም ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት
2) የካፑቺኒ ወንድሞች ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በመንደፈራ
3) የቅዱስ ፍራንቸስኮስ መለስተኛ ሁለተኛ ደረጃና ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤት በምጽዋ
እንዲዘጉ ወይም በመንግሥት እንዲወሰዱ (እንዲወረሱ) ተደርጓል። ይህን በተመለከተም ተገቢውንና ቀጥተኛውን ተቃውሟችንን እናቀርባለን።
4. በተለያዩ አጋጣሚዎች እንደተገለጸው፣ ቤተክርስትያን የተለያየ ሓሳቦቿን ስታቀርብ የምትጀምረው፣ ማንነቷንና ተልዕኾዋን በመተንተን ነው። ይህም የምትሰብከውንና የምታስተምረውን ዓላማዋ ማንነቷንና ተልዕኮዋን ተከትሎ የሚመጣ ነው። ቤተክርስትያን እናትም መምህርም ነች። መስራቿ ኢየሱስ ክርስቶስ ይፈውስና ያስተምር እንደነበረው ሁሉ፡ ለቤተክርስትያንም እንድትፈውስና እንድታስተምር ሥልጣንን ሰጥቷታል። ዋንኛ ስራዋ አምላካዊዉንና ዘላለማዊዉን ሓቅ ማስተማርና መስበክ ቢሆንም እንኳ፡ የሰው ልጅን በነፍስና በሥጋ የመርዳት ሃላፊነትም አለባት። ይህን ሃላፊነቷንም በተግባር የምትፈጽመው፡ በቤተክርስትያን አጥር ግቢ ውስጥ ብቻ ታጥራ ሳይሆን፣ በትምህርት ቤቶቿና የሕክምና ተቋሞቿ እንዲሁም ባጠቃላይ ለሰው ልጅ ሁለንተናዊ እድገት በምትሰራባቸው ማእከላቶቿ አማካኝነት ነው።
5. አጠቃላይ የሁለት ሺ ዓመት ታሪኳና ጉዞዋ በግልጽ እንደሚያሳየው፣ ይህ ተግባሯ ከባህሪዋና ከተልእኾዋ አኳያ የሚመነጭ መብትና ግዴታ እንዳላት ጠንቅቃ ትረዳለች። ክርስትያናዊ የእምነት ትምህርትን ስታስተምር፡ ሰብአዊ እውቀትንና እድገትን የምታስተምርበትና የምታካሂድበት ትምህርት ቤት፣ ከዚህ ጋር የሚያያዝ ተንቀሳቃሽና የማይንቀሳቀስ ንብረትን የማፍራትና የማካሄድ መብት አላት። ይህ መብትም በአምላክ የሚሰጥ ባህርያዊ መብት ስለሆነ፣ በማንኛውም አካል በጎ ፍቃድ ወይ ፍላጎት የሚቸር ወይ የሚሰጥ ወይም የሚከለከል አይደለም። ይህ የጸና እውነታም፣ በምንም መልኩ የማይደፈር መብት ስለመሆኑ አያጠያይቅም።
6. ከጥንት ከጥዋቱ በመላው ዓለም እያዘወተረችው ያለው፣ ማንኛውንም ሰብአዊና መንፈሳዊ ዕውቀትን የሚያሳድግና የሚያበለጽግ፣ ከሙዓለ-ሕፃናት እስከ የዩኒቨርስቲ ደረጃ ድረስ የሚያስተምሩ የተለያዩ ተቋማትን መመስረትና ማካሄድ መብቷና ግዴታዋ ነው። ለምን ቢባል መምህር ናትና ነው። እነኝህ በቤተክርስትያን የሚካሄዱ ተቋማት ዓላማቸው ምንድን ነው? ከተባለ፦
ሀ) የሰው ልጆችን ኅሊና በመኮትኮትና በመመልመል ፣ በኅብረተሰብና በሀገር ውስጥ በብቃትና በተገቢ ሁኔታ አስፈላጊውን ገንቢ ሚና የሚያበረክቱ ብቁ ዜጎች ይሆኑ ዘንድ፣ ስለ ፍትሕ ሰላም መብትና ነጻነት ሓቀኝነትና ወንድማማችነት . . . የሚማሩበት ነው፣
ለ) ወላጆች ለልጆቻቸው ብቁ የሆነ ትምህርትን የመምረጥ ያላቸውን ማንም ሊገፍፋቸውና ሊቀማቸው የማይችልን ባህርያዊና ተፈጥሯዊ መብት ይከበርላቸው ዘንድ፣ ትውልድን በማነጽና የበሰለ ዜጋን በማፍራት ረገድ የበኩሏን አስተዋጻኦ ለማድረግ፣
ሐ) ዜጎች በሥልጣኔና በዕውቀት እንዲያድጉ ለማገዝ፣ በበለጠውና የዘመናት ልምድ ማካበቱ በተመሰከረለት የቤተክርስትያን ሃብታም ልምድና ተሞክሮ እንዲጠቀሙ ለማድረግና ለማስቻል፣
መ) ቅኑና ብቁ የሆነ ለሰው ልጆች እድገት ከመትጋት ውጭ፣ እኒህ የቤተክርስትያን የትምህርት ተቋሞች፣ ሌላ ከዚህ ውጭ የሆነ ድብቅ አላማ ሆነ አካሄድ እንዳልነበራቸው እንደሌላቸውም፣ በትምህርት ተቋማቱ ውስጥ ተምረው፣ ብርቅና ድንቅ ይዞታዉን ያጣጣሙ፣ የተለያዩ የእምነትና የሃይማኖት እንዲሁም የህይወት ዘይቤዎችን የሚከተሉ፣ በሃገር ውስጥና በሃገር ውጭ በተለያዩ ሃገራት ተዘርግተው የሚገኙት ዜጎች ህያው ምስክሮች ናቸው።
የእምነት ማእከላትና የትምህርት እድገት በታሪኽ አዃያ
7. የትምህርት ታሪኽንና አመጣጡን እንዲሁም አስተዳደጉን በመላው ዓለም ስናጤንና ስናጠና፣ አንድ በፍጹም ልንክደው የማንችል ሓቅ ቁልጭ ብሎ ይታያል። ከጥንት ከጥዋቱ የትምህርትና የሥነጽሑፍ መኮትኮቻና ማሳደጊያ ቦታዎች የሃይማኖት ተቋሞች ሲሆኑ፣ በተለይም ቤተክርስትያንና መስጊዶች ለትምህርት እድገት የነበራቸው አስተዋጽኦና ገንቢ ሚና በቀላል የሚገመት ብቻ ሳይሆን እጅግ አስደናቂና አንጸባራቂ ምዕራፍን የያዘ ነው።
የሃገራችንን ታሪክ ወደኋላ ተመልሰን ስንመለከትም፣ የኦርቶዶክሳዊት ተዋህዶ ቤተክርስትያን ጥንታዊ ገዳሞችና ደብሮች፣ እንዲሁም ጥንታዊ መስጊዶች፡ ከጽሑፍና ከንባብ አኳያ፡ ጥንታዊ ታሪኽንና ትምህርትን በማቀብ ረገድ የነበራቸው ሚና ከፍተኛ ነው፣ ባጭር አገላለጽ የዚህ ህዝብንና ሃገርን ባህላዊ ሕንጸትንና ለማንነቱና ለምንነቱም መሰረትን ያስቀመጠ ገንቢ ሚና ተጫውተዋል።
8. የኤርትራ ዘመናዊ ትምህርት ውልደትና እድገት በሚገለጽበትና በሚተነተንበት ወቅትም፣ ካቶሊካዊ ትምህርት ቤቶቻችን እንዲሁም ቤተክርስትያናችን ባጠቃላይ በዚህ ረገድ፣ እጅግ ደማቅና አንጸባራቂ ቦታ እንዳላት ማንም ሰው የሚያዉቀው ፍንትዉ ብሎ የሚታይ ሓቅ ነው። በአፍሪካ ምድር ለመጀመርያ ግዜ የኅትመት ጥበብን በማስተዋወቅ፣ በሃገራችን የትምህርትና የጽሕፈትን በር የከፈተችና የትምህርትን ጉዞ ያፋጠነች ቤተክርስትያን ነች።
በዓዲወግሪ [ሳን ጆርጆ]፣ በሠገነይቲ [ስኮላ ኣርተ መስቲየሪ ሳን ሚኬለ]፣ በዓድቐይሕ፣ በከረን[ሳልቫጎ ራጊ]፣ በኣሥመራ [ስኮላ ቪቶሪዮ] በጣልያን ግዛት ዘመን ለሃገራችን ሰዎች መማርያ የተመሰረቱ ትምህርት ቤቶች ነበሩ፣ እነኝህም በቤተክርስትያን ወይም በቤተክርስትያን ሰዎች የሚተዳደሩና የሚካሄዱ የነበሩ ናቸው። ከሁለተኛ የዓለም ጦርነት በኋላም በዝች በዘመናዊቷ ኤርትራ የተመሰረቱት በተለይም በርእሰ ከተማችን በአሥመራ የተመሰረቱትና የተቋቋሙት የትምህርት ማእከላት ለአብነት ለመጥቀስ፦ ኮምቦኒ ኮሌጅ፣ አሥመራ ዩኒቨርስቲ፣ ኮለጆ ላሳል፣ ኮለጆ ቅድስት ሓናና፣ በቀትር ህጻናትን በምሽት ደግሞ ጎልማሶችን የሚያስተምረው የቅዱስ በርናርዶስ ትምህርት ቤትና . . . ሌሎችም ነበሩ። በተለይም በ 1965ዓ.ም (እ.ኤ.ኣ) ለትምህርት ልዩ ፍቅር በነበራቸው በተወዳጁ ብፁዕ አቡነ ኣብርሃ ፍራንስዋ አነሳሽነት እስከ 70 የሚሆኑ ትምህርት ቤቶች በተለያዩ ቀየዎች በመላዉ ኤርትራ ተመስርተውና ለረዢም ዓመታት ብዙ ኤርትራዉያን ሕፃናትን በትምህርት ገበታ እንዲሳተፉ አስችለው እንደነበር ማስታወስ ተገቢ።
ከጣሊያን የአገዛዝ ዘመን ጀምሮ፣ ዘመናዊ አስተዳደርንና የአማማር ዘዴንና ዘይቤን፣ ፖለቲካዊ ጉዞንና ስነጽሑፋዊ ፈጠራን እንዲሁም የቋንቋን ዕድገት በተመለከተ ረገድ የተካሄደን የህዝባችን የመጀመርያ ተግባራቶች በብዛት በስኬት የተካሄዱት፣ በቤተክርስትያን ተቋሞች በተማሩ ልጆቻችን ብርታት ነው። ይህም ለዘመናዊቷ ኤርትራ መሰረት ሆኗል። በዝች ሃገራችን የፖለቲካ ሂደት ጅማሬም ሆነ በፖለቲካዊና በነጻነት የትግል ጉዞ ሂደትም፣ በቤተክርስትያን ትምህርት ቤቶች ውስጥ የተማሩ ሰዎች ሚና የራሱን ትልቅ ምዕራፍ የያዘ ነው።
9. በታሪኽ ይህን የመሰለ ትልቅ ሚናና ምእራፍ ያበረከቱትን የእምነት ተቋሞችና ማእከሎች፣ በተግባር በትምህርቱ ዘርፍ ያስመዘገቡትን ድልና ስኬት መቀማትና መካድ፣ የትምህርቱ ዘርፍን “ኣይመለከታችሁም” ብሎ ማለት ታድያ ከምን ይቆጠራል? ይህን አካሄድ ከእምነትና ከሃይማኖት ጋር መጻረር ከማለት ውጭ ሌላ ምንም ዓይነት መግለጫ ሊገኝለት አይችልም። እምነትንና ፈሪሃ እግዚአብሄርን ከሚያስተምሩ ማእከላት ሕፃናትንና ወጣቶችን ነጥለንስ፣ ለዝች ሃገር ምን ዓይነት አዲስ ትውልድ እንድናፈራላት ነው የታሰበው ማለት ነው?
10. በተለይም የካቶሊክ ቤተክርስትያን ትምህርት ቤቶችን በተመለከተ፡ ይህን መሰሉን ውሳኔ ለመወሰን የሚያስገድድ አንዳችም ዓይነት የትምህርት ሥርዓትን የማዛባት፣ ወይም ሕግን የመጣስ፣ ማለትም የትምህርት ጥራትንና ብቃትን እንዲሁም አማማርን ማለትም የመማር ማስተማር ሂደትን በተመለከተ፣ በትምህርት ቤቶቻችን የተገኘ እክል ወይም ከተገቢው መሥመር የማፈንገጥ አዝማሚያ፣ በመንግሥት በኩል እንደ ማስረጃነት አልተጠቀሰብንም። ሊጠቀስ የሚችል እክል ወይ ጉድለትም በጭራሽ የለንም። ትምህርት ቤቶቻችን ዛሬ ብቻ ሳይሆን ከምስረታቸው ጀምሮ፣ በዕለታዊ አሰራራቸውና እንዲሁም ተማሪዎቻቸው በሃገራዊ ፈተናዎች የሚያስመዘግቡት ድንቅ ውጤት፣ በብቃታቸው ሆነ በዓይነታቸው የተመሰገኑና የተመሰከረላቸው በመሆናቸው፣ ይህን ለመሰለው አሉታዊ የመንግስት ውሳኔ ሳይሆን፣ ሽልማትና ማበረታታት ሊቸራቸው የሚገባ መሆኑን፣ የሚመለከተው የመንግሥት አካል ማለትም የትምህርት ሚኒስቴር በየግዜው የሚቀርቡለትን ሪፖርትና በአርካይቮቹ ይዟቸው የሚገኙት መዛግብቶቹ ምስክር ናቸው።
11. እንደ የቤተክርስትያናችን ግንዛቤ፡ ትምህርትን በተመለከተ፡ የመንግሥት ግዴታና ኃላፊነት፡ ዜጎች ሁሉ አስፈላጊዉንና ብቁ የሆነን የትምህርት ዕድል ማግኘታቸውን ማረጋገጥ፣ መብትና ግዴታቸውንም መግለጽ፣ ሕፃናት ተገቢዉን ትምህርት እንዲያገኙ ማድረግ፣ የትምህርት ተቋሞች በተገቢው ሁኔታ እያስተማሩ ናቸው ወይስ አይደሉም ብሎ መቆጣጠር፡ በሃገር ደረጃ የሚወጡ መመሪያዎችንና የትምህርት ሥርዓትን እየተከተሉ ናቸው ወይስ አይደሉም ብሎ መቆጣጠር ነው። የሚወጣው የትምህርት መመሪያም የመማርና ማስተማሩን ሂደት የሚያግዝ ይሆን ዘንድ፣ መበረታታት የሚገባዉን አካል ማበረታታት፣ ሊታረም የሚገባዉን አካልም በማረም፣ በግል ይሁን በቤተክርስትያን አማካኝነት የሚካሄድን የመማርና የማስተማር ሂደት ወደ ፊት ይበልጥ ይራመድ ዘንድ ማስቻል ነው።
የቤተክርስትያንና የወላጆች መብት
12. መንግሥት በዓለምአቀፍ ደረጃ ተቀባይነት ያለዉን የወላጆችንና የቤተክርስትያንን መብት ማወቅና ማክበር ግዴታው ነው። ወላጆች ለልጆቻቸው ያሻቸውን የትምህርት ዓይነትና የአማማር ዘዴን የመምረጥ፣ ቤተክርስትያንም በውስጧ ያሉ ልጆቿን ሆነ ትምህርት ቤቶቿን መርጠው የሚመጡ ማናቸውም ዜጎችን በነጻነት የማስተማር መብቷና ግዴታዋ በአግባቡ ሊታወቅና ሊከበር ይገባል።
13. ከዚህ ባሻገር የወላጆችንና የቤተክርስትያንን መብት በሚጻረር መልኩ እርምጃዎችን መውሰድ ተቀባይነት የሌለውና እጅጉኑ ጎጂ አካሄድ ነው። ሕፃናትንና ወጣቶችን ከወላጆቻቸው፣ በሞራልና በሥነምግባር ከምታንጻቸው ቤተክርስትያንና የእምነት ቤታቸው በመነጠል፣ ይህን መሠረታዊና ባህርያዊ መብትንና ግዴታን ችላ በማለት የሚኬደው፣ “ወጣቶችን ለመያዝ” የሚደረግ አካሄድ፤ ሲቪል ኅብረተሰብ ሆነ የእምነት ማእከላት ሕግና ሥርዓትን ተከትለው፣ ለሰው ልጆች ይጠቅማል ብለው ያሰቡበትን አሰራራቸውን እንዳይተገብሩ የሚገታበት አካሄድ ሁሉ ነጻነት የለበትም፤ በዚህ ሁኔታ ዓለም አቐፋዊ የሰው ልጆች መብትም አልተከበረም ማለት ነው። ማንኛውም ስራ በመንግስት አካል ብቻ የሚያዝበት አሰራርና አካሄድ፣ የግልንና የሰብአዊ ነጻነትንና አካሄድን የሚገታ አካሄድ ነው፣ ነጻነትና መብት ባልተከበረበት ደግሞ፣ ሰላም ሆነ መረጋጋት እንዲሁም እድገት ሊመጣና ሊገኝ አይችልም።
እንግዲያዉኑስ በዚህ መርህ መሠረት፣ በየጊዜው ከተቋሞቻችን አንጻር የሚደረገው መብትን የመጋፋት የመርገጥና የመጣስን ውሳኔና ተግባር እኛ እንደግለሰቦች፣ እንደ ኤርትራዉያን ዜጎችና እንደ ካቶሊካዉያን መጠን በጭራሽ አንቀበለዉም፤ ዜጎችና አማንያን እንደመሆናችን መጠን ያለንን መብትና ግዴታም ችላ አንለዉም፣ ይህ እላይ የጠቀስነውን መብታችንን ስንገፈፍ ወይም የጠቀስናቸውን ግዴታዎቻችንን ሳንወጣ ስንቀር፣ በዋነኛነት የሚጎዳው በዚች ሃገራችን ውስጥ ያለው ዜጋ ወይ ኅብረተሰብ ነው፣ ቀጥሎም ሃገር እንደ ሃገርነቷም ትጎዳለች። በተቋቋሙበት ዓላማና በተግባር በተፈተኑበት አሰራራቸው መሰረት፣ ተቋሞቻችንን በሙሉ ለህዝብና ለሃገር ጥቅም መሆኑን ስለምንተማመንባቸው፤ እነዚህ ተቋሞች ሲወረሱና የቤተክርስትያን መብት ሲደፈር በዋነኛነት የሚጎዳው ሕዝብና ሃገር መሆኑን መረዳትና መታወቅ አለበት።
መደምደሚያ
14. በዚህች አገራችን ውስጥ አሁን ያለንበትን ሁኔታና ያለፈውን ታሪኽ በጥልቀት ከመረመርን በኋላ፣ በተለይም በትምህርት ረገድ የቤተክርስትያን ታሪኽ አንጸባራቂ መሆኑን እንጂ አንዲትም ጥቁር ነጥብ ወይም ጉድፍ እንደማይገኝበት አፋችንን ሞልተን መናገር እንችላለን። ስለሆነም በአሁኑ ወቅት፦
ሀ) ከትምህርትና የሕክምና ተቋሞቻችን አንጻር የሚተላለፈው ውሳኔና፣ ውሳኔውን ተከትሎ የሚካሄደው ተግባር፣ በዋነኛነት የቤተክርስትያንን መብትና የእምነት ነጻነት የሚጻረር ተግባር፣ በእምነቷ በማንነቷና በአገልግሎቷ ውስጥ ጣልቃ ገብነትና ህልውናዋን የሚፈታተን መሆኑን እየገለጽን፡ ይህ ተግባር ዳግም ተመርምሮ በአፋጣኝ እንዲቆም እንጠይቃለን፣
ሁ) የቤተክርስትያን ተቋማት የኤርትራ ልጆች ተቋም እንደመሆኑ መጠን፣ መደበኛውንና ድንቁን የትምህርትና የሕክምና አገልግሎቱን በነጻነትና በታታሪነትን ይቀጥል ዘንድ ዕድል እንዲሰጠው እንጠይቃለን፣
ሂ) ሊታረም ወይ ሊወገድ የሚገባው ማንኛውም እንከን ካለም፣ በጋራ ውይይትና የመግባባት መንፈስ እንዲፈታ ማድረግ መልካም ብቻ ሳይሆን ብቸኛው መንገድ መሆኑን እናስገነዝባለን።
15. እንግዲያዉኑስ ቤተክርስትያን ለዘመናት ባካበተችው ልምድ፣ ረዢም ትዉፊትና ዓቅም ኣኳያ፣ ለሰው ልጆች እድገት ወሳኝ ሚና ባለው በትምህርቱ ዘርፍ፣ የመንግስትን መመሪያ በመከተል፡ የተለያዩ ትምህርት ቤቶችን መክፈትና ማካሄድ፣ ከተልእኾዋ አንዱ ክፍል መሆኑን መግለጽ ትወዳለች። ይህን ተልእኮዋን የሚቃወም ማንኛውም ዓይነት ውሳኔ ወይ ሂደት ነጻነቷንና መብቷን እንደገፈፋት ትረዳለች፣ ይህን መብቷን ዳግም እስክትጎናጸፍና ነጻነቷን እስክትጨብጥ ድረስ ከመእምናኖቿ ጋር ሆና ወደ አምላክ ያለማቋረጥ ጸሎቷንና ምህለላዋን ታሳርጋለች፣ በህጋዊ መንገድም ለሚመለከተው አካል መብቷ ይከበር ዘንድ ስሞታዋን እያቀረበች “ጥያቄዋ ይመለስ መብቷም ይከበር ዘንድ አቤቱታዋን ሳታሰልስ ከማቅረብ አትቦዝንም።
አምላክ ሃገራችንን፣ የሰላምና የፍትህ ሃገር የርትዕና የፍቅር ሃገር ያድርግልን።
ካቶሊካውያን ጳጳሶች
1. ኣቡነ መንግሥተኣብ ተስፋማርያም ፣ ሊቀጳጳስ ዘመንበረ ኣሥመራ
2. ኣቡነ ቶማስ ዖስማን፣ ጳጳስ ዘመንበረ ባረንቱ
3. ኣቡነ ኪዳነ የዕብዮ፣ ጳጳስ ዘመንበረ ከረን
4. ኣቡነ ፍቅረማርያም ሓጎስ፣ ጳጳስ ዘመንበረ ሠገነይቲ
ኮፒ ለ፦
1. ዞባዎች አስተዳደ ሚንስትሪ
2. ሃይማኖታዊ ጕዳዮች ጽሕፈት ቤት
3. ህ.ግ.ደ.ፍ. ጽሕፈት ቤት
4. ደቡብ ዞባ አስተዳደር
5. ዓንሰባ ዞባ አስተዳደር
6. ሰሜናዊ ቀይ ባሕር ዞባ አስተዳደር
https://www.vaticannews.va/ti/church/ne ... zione.html