Page 1 of 1
ኃይለሚካኤል (ሊንጎ) - “‘ኣግኣዝያን’ የቕዥቢዎች የቅዠት ፖለቲካ ነው።”
Posted: 10 Sep 2019, 04:06
by Meleket
የትግራይ የከሰሩ የህወሓት ቦለቲከኞች
“ትግራይ-ትግርኚ” የሚባል ፍልስፍና መኽሸፉን ሲገነዘቡ!
“ዓባይ-ትግራይ” የሚባል የህልም ሩጫ ከንቱ መሆኑን ሲያጤኑ!
ከታላቋ ኢትዮጵያ የሥልጣን ኮረቻ በካልቾ ተጠልዘው መቐለ ከተወሸቁ በኋላ፡ ዛሬ ዛሬ ዓይናቸውን በጨው ታጥበው፡
“የአይንህ ቀለም አላማረንም” ያሉትን ኤርትራዊ “ኣግኣዛዊ ወንድማችን ነህ” ለማለት እየዳዳቸው ነው እፍረት የማያውቁ ከንቱ ቦለቲከኞች!
ለዚህም ነው አንዱ ምርጥ አንደበተ ርቱዕ ኃይለሚካኤል (ሊንጎ) የተባለ ገጣሚ ኤርትራዊ ታጋይ፡ በዚህ ከንቱ ቫይረስ የተለከፉ ምስኪኖችን፡ በጥንቱ “ፖስትካርድ” እንደምናዉቀው ቢኒዓምር ነጫጭ ጥርሶቹን በፈገግታ እያሳየ፡ ባጠቃላይ እንዲህ ያላቸው፦
https://tigrigna.voanews.com/a/%E1%8A%A ... 73480.html
‘ኣግኣዝያን’ የቕዥቢዎች የቅዠት ቦለቲካ ነው። (አራት ነጥብ)
ይሰማል!
ንሓቂ ምስ ገለጽና ንሓሶት ነሸቝርራ፣
ንጸላኢ ጥምረትና መሬት ነንገርግራ፣
ፍለጡና በሉ ንሕና ኢና ኤርትራ ራ ራ ራ!
Re: ኃይለሚካኤል (ሊንጎ) - “‘ኣግኣዝያን’ የቕዥቢዎች የቅዠት ፖለቲካ ነው።”
Posted: 11 Sep 2019, 10:39
by Meleket
የቕዝቢዎቹ ኣግኣዝያን ቕዠት ቀጥሏል። ቁንጯኛቸው እንዲህ ይላል፦
አማርኛ ኩሽቲክ ነው። 40%% የግእዝ ፊደላትን ሊያነብ ኣይችልም። አማሮች ላቲን ቢጠቀሙ ይሻላቸዋል።
ያገሬ አምባሳደሮች ደግሞ እንዲህ ይሉታል፦
ኣቶ ሑሴን ሉባክ፣ ጀግናዉ የኣግኣዚያን ውጥንን አክሻፊ እንዲህ ይላል፦
መጀመርያ VOA ዓለም ውስጥ ካሉት 13 ሐቀኛ መገናኛ ብዙሓን አንዷ ናት። . . . ኣግኣዚያን ሲባል “ሊንጎ” እንዳለው ግእዝ መሰረታቸው የሆነን ትግረን ትግርኛንና አማርኛን ወዘተን ሊያጠቃልል ይገባው ነበር። ነገር ግን አንዲትም ቀን ይህ ኣግኣዚያኖች ስለ ኣማርኛ ሲያወሱ ኣልተሰመሙም። በዩቲዩብ ገንዘብ መሰብሰብያ እየተጠቀሙበት እንዳይሆኑ ያሰጋል።
ግእዝ መሰረታችን የሆነ አንድ እንሁን የምትሉ ከሆነ፣ ዓረብኛ ተናጋሪዎች አንድ ሆነዋል እንዴ? ዓፋርኛ ተናጋሪዎች አንድ ሆነዋል እንዴ? ግእዝ መሰረታቸው የሆኑ ሁሉም እንዲህ ሲሉ ስላልሰማን፣ እኛ ኢስት ኩሺትኮች ነን ብለን ከኦሮሞ፣ ሶማል፣ ሳሆና አፋር ወዘተ ጋር ሆነን ሌላ ትግል በጀመርን ነበር! ግን....
ሊንጎም እንዲህ ብሏል፦
ያንተን በጎ ተግባሮች መግለጽ ወግ ነው፣ ነገር ግን ሌሎችን እያንቋሸሸኽ መሆን የለበትም። በዚህ ዘመን ለጥላቻ ብሎ የተነሳ ድርጅት ካለ የዚህ ድርጅት ተከታይና ደጋፊ ከመሆን ይልቅ ይህን ድርጅት መቃወሙን እመርጣለሁ።
https://tigrigna.voanews.com/a/%E1%8A%A ... 78084.html
እኛ ደግሞ እንዲህ አድርገን እንቀጥላለን ‘ኣግኣዝያን’ የሚባለው ቡድን ኤርትራዉያን ስለ ድንበራቸው፣ ስለ ልዑላዊ መሬታቸው ስለ ሕገ መንግሥታቸው ጥያቄን እንዳያነሱ ለማረሳሳትና ለማዘናጋት የተፈጠረ ቡድን ከሆነስ ማን ያውቃል?ጠርጥር!!!
“ኣናፍራ ቆቓሕ ዘይፈልጥ ኣይ ሃዳናይን!” ይላሉ ያገራችን ሰዎች “የቆቅን ጠባይ የማያውቅ አዳኝ ሊሆን አይችልም!” እንደማለት ነው፡ አግኣዝያንን በጀርባ ሆነው የፈጠሩ አካላት ነቅተንባችኋል፣ እኛ ኤርትራዉያን!
ለማንኛዉም እንኳን ለቅዱስ ዮሃንስና አዲስ የግእዝ ዓመተ ምሕረት በሰላም አደረሰን!!! 
Re: ኃይለሚካኤል (ሊንጎ) - “‘ኣግኣዝያን’ የቕዥቢዎች የቅዠት ፖለቲካ ነው።”
Posted: 11 Sep 2019, 13:38
by quindibu
የነወያኔ ፍየሏን በግ ናት ብለን ከሰየምናት በግ መሆን ትችላለች ዐይነት ሙግት (ፍልስፍና) የሰዎቹን የአስተሳሰብ ደረጃ ፍንትው አድርጎ ከማሳየት አልፎ የሚፈይደው ነገር አይኖርም፥ መሬት ጠፍጣፋ ናት ብሎ ማመን ግለሰባዊ ምርጫ ሊሆን ይችላል፥ ይህንን ዕብደት ግን የናሳ (NASA) ጠፈር ተመራማሪዎች ካልተቀበሉት ድርጅቱን አፍርሼ ተመራማሪዎቹን ሳይወዱ በግዳቸው የኔ እምነት ተከታይ አደርጋለሁኝ ብሎ ያዙኝ ልቀቁኝ ማለት ማንም ጤነኛ አእምሮ ላለው ሰው የሚጨበጥ አይደለም፥፥ ድንቁርናቸውን እንደ ሜዳልያ ደረታቸው ላይ ለጥፈው ከሚዞሩት የትግራይ ምሁራን ነን ባዮች ይህ የማይጠበቅ አይደለምና ሊገርመን አይገባም::
Re: ኃይለሚካኤል (ሊንጎ) - “‘ኣግኣዝያን’ የቕዥቢዎች የቅዠት ፖለቲካ ነው።”
Posted: 11 Sep 2019, 13:51
by eden
This is a clash of ideas within Eritrea Tegaru primarily. It wouldn't even be an issue if the clash had been eri Tegaru vs eth Tegaru. So bringing weyane here is not dealing with the issue. That's how it looks to me.
Re: ኃይለሚካኤል (ሊንጎ) - “‘ኣግኣዝያን’ የቕዥቢዎች የቅዠት ፖለቲካ ነው።”
Posted: 11 Sep 2019, 14:21
by quindibu
eden wrote: ↑11 Sep 2019, 13:51
This is a clash of ideas within
Eritrea Tegaru primarily. It wouldn't even be an issue if the clash had been eri Tegaru vs eth Tegaru. So bringing weyane here is not dealing with the issue. That's how it looks to me.
የነወያኔ ፍየሏን በግ ናት ብለን ከሰየምናት በግ መሆን ትችላለች ዐይነት ሙግት (ፍልስፍና) የሰዎቹን የአስተሳሰብ ደረጃ ፍንትው አድርጎ ከማሳየት አልፎ የሚፈይደው ነገር አይኖርም፥