Page 1 of 1

@Oromia: አፋን ኦሮሞ የፌደራል የሥራ ቋንቋ እንዳይሆን ሕገ-መንግስቱ አይከለክልም፡፡ ስለዚህ ሕገ-መንግስቱን ማሻሻል ሳያስፈልግ አፋን ኦሮሞ የፌደራል የሥራ ቋንቋ ማድረግ ይቻላል፡፡

Posted: 28 Aug 2019, 15:58
by AbebeB
አማርኞች አፋን ኦሮሞን የፌደራል የሥራ ቋንቋ ለማድረግ ሕገ-መንግስቱ መሻሻል አለበት በማለት በግርግር ውስጥ አንድ ዳቦ ጠፋ ለመጫወት ይጥራሉ፡፡ እውነቱ ግን ሕገ-መንግስቱ አማርኛን ደነገገ እንጂ አፋን ኦሮሞን አልተቃወመም፡፡

ስለዚህ እንደ አስቸኳይነቱ መጠን ሕገ-መንግስት ማሻሻል ገለ-መሌ ሳንል አፋን ኦሮሞ የፌዴራል የሥራ ቋንቋ መሆኑን ማወጅ ብቻ ነው፡፡ ያውም ለኢትዮጵያ አፍቃሪዎች ሲባል እንጅ ይህ የኦሮሞን ሕዝብ ብዙም አያስጨንቀውም፡፡ ይልቁንስ ወደ ዋናው ግባችን እንድንጣደፍ ያግዘናል፡፡