Page 1 of 1

"ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ኮሌጆች በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ ተገኙ!" No kidding! ሃሃሃ! ቅቅቅ!

Posted: 28 Aug 2019, 11:05
by Revelations
You can't make this up! :lol: :lol: :lol:

ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ እንደተደረሰባቸው፣ የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡

ኤጀንሲው ከተለያዩ ግለሰቦች በደረሰው ጥቆማ መሠረት ወደ ክልሉ ተንቀሳቅሶ የለያቸው እነዚህ 11 ተቋማት በድኅረ ምረቃና በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን እየተቀበሉ እንደሚያስተምሩ ለሪፖርተር የገለጹት፣ የኤጀንሲው የኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ገረሱ ናቸው፡፡

ከኤጀንሲው ፈቃድ ሳያገኙ ሊያስተምሩ የተገኙት 11 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በአገር ውስጥ የማይታወቁና እንግዳ መጠሪያ ያላቸውና ከውጭ የገቡ እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡

‹‹በተደጋጋሚ በደረሰን ጥቆማ መሠረት ለማጣራት ወደ ክልሉ ስናመራ የጠበቅነው አንድ ተቋም ብቻ ነበር፡፡ ስንደርስ ግን 11 ሆነው አገኘናቸው፡፡ በወቅቱ ምንም ማድረግ ስላልቻልን ለክልሉ መንግሥት ስለሁኔታው በማስረዳት የክልሉን ነዋሪዎች ከሕገወጦች እንዲጠብቅ ደብዳቤ ጻፍን፤›› የሚሉት አቶ ታረቀኝ፣ ለክልሉ ደብዳቤ ከተጻፈ ስድስት ወራት የተቆጠረ ቢሆንም ምንም ዓይነት ምላሽ ለኤጀንሲው አለመድረሱን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡

ተቋማቱ ክልሉ ውስጥ ገብተው ሲያስተምሩ ምን ያህል ጊዜያት ማስቆጠራቸውን፣ እስካሁን ምን ያህል ተማሪዎችን ማስመረቃቸውንና እያስተማሩ መሆናቸውን በውል እንደማይታወቅ፣ በቀጣይ በሚደረግ ማጣራት ይፋ እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡ ጉዳዩ ከምን እንደደረሰም በቅርቡ ወደ ክልሉ ተንቀሳቅሰው ማጣራት እንደሚደረግም አክለዋል፡፡

https://www.ethiopianreporter.com/article/16573

Re: "ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ኮሌጆች በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ ተገኙ!" No kidding! ሃሃሃ! ቅቅቅ!

Posted: 28 Aug 2019, 11:54
by Revelations

Re: "ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ኮሌጆች በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ ተገኙ!" No kidding! ሃሃሃ! ቅቅቅ!

Posted: 28 Aug 2019, 19:44
by Ethoash
ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ኮሌጆች በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ ተገኙ!" No kidding! ሃሃሃ! ቅቅቅ!
Realbull

if Harvard University come and open collage in ጋምቤላ ክልል... that make Harvard University ከየት እንደመጡ ያልታወቁ ሕገወጥ ኮሌጆች...


The 10 Best Hospitals in the World
The Mayo Clinic. The Rochester, Minnesota–based Mayo Clinic has provided patients with comprehensive medical care for over 150 years. ...
Cleveland Clinic. ...
Singapore General Hospital. ...
Johns Hopkins Hospital. ...
Charité ...
Massachusetts General Hospital. ...
Toronto General Hospital. ...
University of Tokyo Hospital.

if those hospital come and open hospital in Gamablle our realbull he will say ከየት እንደመጡ ያልታወቁ ሕገወጥ hospital how dare they give world class health care to ጋምቤላ ክልል without jump the bureaucratic loop and get their paper..