"ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ኮሌጆች በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ ተገኙ!" No kidding! ሃሃሃ! ቅቅቅ!
Posted: 28 Aug 2019, 11:05
You can't make this up!
ከየት እንደመጡ ያልታወቁ 11 ሕገወጥ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጋምቤላ ክልል ሲያስተምሩ እንደተደረሰባቸው፣ የከፍተኛ ትምህርት አግባብነትና ጥራት ኤጀንሲ አስታወቀ፡፡
ኤጀንሲው ከተለያዩ ግለሰቦች በደረሰው ጥቆማ መሠረት ወደ ክልሉ ተንቀሳቅሶ የለያቸው እነዚህ 11 ተቋማት በድኅረ ምረቃና በተለያዩ የትምህርት ፕሮግራሞች ተማሪዎችን እየተቀበሉ እንደሚያስተምሩ ለሪፖርተር የገለጹት፣ የኤጀንሲው የኮሙዩኔኬሽን ጉዳዮች ዳይሬክተር አቶ ታረቀኝ ገረሱ ናቸው፡፡
ከኤጀንሲው ፈቃድ ሳያገኙ ሊያስተምሩ የተገኙት 11 የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት፣ በአገር ውስጥ የማይታወቁና እንግዳ መጠሪያ ያላቸውና ከውጭ የገቡ እንደሆኑ ዳይሬክተሩ ገልጸዋል፡፡
‹‹በተደጋጋሚ በደረሰን ጥቆማ መሠረት ለማጣራት ወደ ክልሉ ስናመራ የጠበቅነው አንድ ተቋም ብቻ ነበር፡፡ ስንደርስ ግን 11 ሆነው አገኘናቸው፡፡ በወቅቱ ምንም ማድረግ ስላልቻልን ለክልሉ መንግሥት ስለሁኔታው በማስረዳት የክልሉን ነዋሪዎች ከሕገወጦች እንዲጠብቅ ደብዳቤ ጻፍን፤›› የሚሉት አቶ ታረቀኝ፣ ለክልሉ ደብዳቤ ከተጻፈ ስድስት ወራት የተቆጠረ ቢሆንም ምንም ዓይነት ምላሽ ለኤጀንሲው አለመድረሱን ለሪፖርተር ገልጸዋል፡፡
ተቋማቱ ክልሉ ውስጥ ገብተው ሲያስተምሩ ምን ያህል ጊዜያት ማስቆጠራቸውን፣ እስካሁን ምን ያህል ተማሪዎችን ማስመረቃቸውንና እያስተማሩ መሆናቸውን በውል እንደማይታወቅ፣ በቀጣይ በሚደረግ ማጣራት ይፋ እንደሚሆን አስረድተዋል፡፡ ጉዳዩ ከምን እንደደረሰም በቅርቡ ወደ ክልሉ ተንቀሳቅሰው ማጣራት እንደሚደረግም አክለዋል፡፡
https://www.ethiopianreporter.com/article/16573