Page 1 of 1

በታከለ ኡማ ፈቃድ ከባድ የደን ጭፍጨፋ በመሀል አዲስ አበባ እየተካሄደ ነው!

Posted: 15 Aug 2019, 13:06
by Revelations
ዛሬ ቦሌ ወረዳ 3፣ ፒኮክ መናፈሻ አካባቢ ከባድ የደን ጭፍጨፋ እየተካሄደ እንደሆነ መረጃ ደረሰኝና ከደቂቃዎች በፊት ወደ ስፍራው ሄድኩ። እንደተመለከትኩት ከአውሮፓ ህብረት ጀርባ ያለው ይህ ጥቅጥቅ ደን ሙሉ ለሙሉ እየተቆረጠ ነው። እርግጥ ቆረጣው የተጀመረው ከሶስት ቀን በፊት እንደነበርና ይህ የባህር ዛፍ ደን እድሜው ከ40- 50 አመት እንደሚገመት የአካባቢው ሰዎች ነግረውኛል።

ቆረጣውን ሲያስተባብር የነበረውን ግለሰብም አግኝቼ ስለጉዳዩ ጠይቄው ነበር። የፍቃድ ደብዳቤ አሳይቶኝ እንዲህ ሲልም መለሰልኝ:

"እነዚህን ለመቆረጥ የደረሱ ዛፎችን እንድንቆርጥ እና ወደ 8,000 ካሬ የሚጠጋው መሬት ላይ መዝናኛ ፓርክ፣ የመኪና ማቆሚያ፣ ሲኒማ፣ የመዋኛ ገንዳ፣ ላይብረሪ፣ ካፌዎች እና ሌሎች አገልግሎት መስጫዎችን እንድንሰራ የፈቀዱልን ም/ከንቲባ ታከለ ኡማ ናቸው። ዛፎቹን ቆርጠን እና ሸጠን ገቢውን ለአ/አበባ አካባቢ ጥበቃ እናስገባለን፣ ቦታውን ደሞ እኛ የአካባቢው ሰዎች እንጠቀምበታለን። ስለዚህ ህገ-ወጥ ቆረጣ እያካሄድን አይደለም። ዛፎቹም በእርጅና ምክንያት እራሳቸው እየወደቁ ነው።"

Re: በታከለ ኡማ ፈቃድ ከባድ የደን ጭፍጨፋ በመሀል አዲስ አበባ እየተካሄደ ነው!

Posted: 15 Aug 2019, 13:14
by Revelations
የአረንጓዴው ፉገራ ትክክለኛ ገፁ ይሄ ነው!






Re: በታከለ ኡማ ፈቃድ ከባድ የደን ጭፍጨፋ በመሀል አዲስ አበባ እየተካሄደ ነው!

Posted: 15 Aug 2019, 13:58
by Revelations
ዛፍ መቁረጥ ፣ ቤት ማፍረስ ፣ ሕዝብ ማስራብ ......


Re: በታከለ ኡማ ፈቃድ ከባድ የደን ጭፍጨፋ በመሀል አዲስ አበባ እየተካሄደ ነው!

Posted: 15 Aug 2019, 14:47
by Ethoash
ባህር ዛፍ መቆረጥ አለበት ያለበለዝያ ምን ጥቅም እናገኛለን። በተቆረጠው ምትክ ሲተከል ስራ ለተካዩ ይፈጥራል ጥቅም እንዳለው ስለሚታዋቅ እንክብካቤ የደረግለታል ። ባህር ዛፍ በከተማ ውስጥ በጣም አደገኛ ነው ባህር ዛፍ ዘይት አለው ። እናም ታውቃላቹሁ ዘይት እሳት ሲነካው እንደሚቀጣጠል ታድያ ቤንዚን ቤት ውስጥ እንደማስቅመጥ ነው የከተማ ውስጥ ጫካ ። በባህር ዛፉ ምትክ ጥዳን ውይራ የአገራችን ዛፎች መተከል አለባቸው።
ዋናው ቁምነገሩ አንድ ዛፍ ሲቆረጥ በምትኩ ፵ መተከል አለብት አለቀ ደቀቀ።