የኦሮሚያ ኮኦፕሬቲቭ ባንክ (Cooperative Bank Of Oromia) አዲስ አበባ ለቡ ቅርንጫፍ ባለፈው እሁድ ለሊት ተዘረፈ
Posted: 06 Aug 2019, 22:03
ባንኩ 2,000,000 (2 ሚሊዮን) ገደማ መዘረፉ ተረጋገጠ!!
የኦሮሚያ ኮኦፕሬቲቭ ባንክ (Cooperative Bank Of Oromia) አዲስ አበባ ለቡ ቅርንጫፍ ባለፈው እሁድ ለሊት ተዘርፎ ማደሩ ታዉቋል። የባንኩ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ በለጠ ዋቅቤካ እዉነት ተዘርፏል ወይ ተብለዉ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ ትክክል ነዉ ባንካችን ተዘርፏል ጉዳዮን ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያካሄደ ነው ብለዋል። ዘራፊዎቹ እነማ ናቸዉ ተብሎ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ የጥበቃ ሰራተኞ ከሌሎች ጋር ተመሳጥረዉ ነዉ ያሉ ሲሆን ጥበቃዎቹ በኤጀንሲ የመጡ ናቸው ስለሆነም የጥበቃ ሰራተኛ ያቀረበልን ኤጀንሲውም ተጠያቂ ይሆናል ብለዋል። እንደ አቶ በለጠ ገለፃ የተዘረፈው ገንዘብ መጠን በውል አይታወቅም ያሉ ቢሆንም ከ1 ሚሊዮን 400,000 እስከ 1 ሚሊዮን 700,000 ብር ተዘርፏል የሚል ግምት ግን አለን ብለዋል። እገንዘብ ማስቀመጫዉ ተሰብሮ እንደተዘረፈ ታውቋል። ቅርንጫፉ ግን አሁን ላይ አገልግሎት እየሰጠ ነው፣ የአገልግሎት መቋረጥም አላጋጠመም ሲሉ ተናግረዋል።

የኦሮሚያ ኮኦፕሬቲቭ ባንክ (Cooperative Bank Of Oromia) አዲስ አበባ ለቡ ቅርንጫፍ ባለፈው እሁድ ለሊት ተዘርፎ ማደሩ ታዉቋል። የባንኩ ኮሚኒኬሽን ዳይሬክተር አቶ በለጠ ዋቅቤካ እዉነት ተዘርፏል ወይ ተብለዉ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ ትክክል ነዉ ባንካችን ተዘርፏል ጉዳዮን ፖሊስ ተጠርጣሪዎችን ይዞ ምርመራ እያካሄደ ነው ብለዋል። ዘራፊዎቹ እነማ ናቸዉ ተብሎ ለቀረበላቸዉ ጥያቄ የጥበቃ ሰራተኞ ከሌሎች ጋር ተመሳጥረዉ ነዉ ያሉ ሲሆን ጥበቃዎቹ በኤጀንሲ የመጡ ናቸው ስለሆነም የጥበቃ ሰራተኛ ያቀረበልን ኤጀንሲውም ተጠያቂ ይሆናል ብለዋል። እንደ አቶ በለጠ ገለፃ የተዘረፈው ገንዘብ መጠን በውል አይታወቅም ያሉ ቢሆንም ከ1 ሚሊዮን 400,000 እስከ 1 ሚሊዮን 700,000 ብር ተዘርፏል የሚል ግምት ግን አለን ብለዋል። እገንዘብ ማስቀመጫዉ ተሰብሮ እንደተዘረፈ ታውቋል። ቅርንጫፉ ግን አሁን ላይ አገልግሎት እየሰጠ ነው፣ የአገልግሎት መቋረጥም አላጋጠመም ሲሉ ተናግረዋል።
