Page 1 of 1

በአማራ ክልል የተሰራው ትልቁ የዘይት ፋብሪካ ስራውን ሊጀምር ወራት ይቀሩታል! ይህ ፋብሪካ አብዛኛውን የአገሪቱን የዘይት ፍጆታ ያሟላ ተብሎ ይጠበቃል::

Posted: 04 Aug 2019, 11:51
by Abaymado

በጎጃም በቡሬ አካባቢ በአማራው ባለ ሀብት አቶ በላይነህ ክንዴ በ 500 ሚልዮን ብር ወጪ የተሰራው የዘይት ፋብሪካ የመጀመርያው ግንባታ ሙሉ በሙሉ ተጠናቅዋል::
ከስድስት ወር በኃላ ስራውን እንደሚጀምር ተገልፅዋል::
ይህ ፋብሪካ ሲጠናቀቅ የሃገሪቷን 60 ከመቶ የዘይት ፍላጎት እንደሚሸፍን ተነግሯል :((ምን ያህል እውነት ይሆን?)
ፋብሪካው ባንድ ቀን ወደ 650,000 ሊትር የpalm ዘይት እና 653,332 ሊትር የአኩሪ አተር: የሱፍና የሌሎችን የቅባት እህሎች ዘይት ማምረት ይችላል:: ባጠቃላይ በቀን ከአንድ ሚልዮን በላይ ሊትር ያመርታል ተብሏል:: በተጨማሪ ወደ 120 ሺ ቶን የተቀነባበረ የሰሊጥ ምርት ወደ ውጭ እንደሚልክ ታውቅዋል::
2000 ሰራተኞችንም እንደሚቀጥር ይጠበቃል::
ትልቁ ችግር ግን የመብራት አቅርቦት እንደሆነ ተገልፅዋል!

!

source -amara mass media

Re: በአማራ ክልል የተሰራው ትልቁ የዘይት ፋብሪካ ስራውን ሊጀምር ወራት ይቀሩታል! ይህ ፋብሪካ አብዛኛውን የአገሪቱን የዘይት ፍጆታ ያሟላ ተብሎ ይጠበቃል::

Posted: 04 Aug 2019, 12:12
by Halafi Mengedi
We will export you oil seeds from Metema Yohannes, Abraha Jira, Tahtay Armachiho, Endabat, Duba Erqi, Adi Arkay and Beida