Page 1 of 1
ትኩረት ያላገኘው የአፋር ወጣቶች የመብት ትግል እና የሚደርስባቸው አፈና
Posted: 20 Apr 2019, 07:23
by Revelations
Please wait, video is loading...
Re: ትኩረት ያላገኘው የአፋር ወጣቶች የመብት ትግል እና የሚደርስባቸው አፈና
Posted: 20 Apr 2019, 07:43
by Ethoash
when i read this kind of የመብት ትግል ... i always happy because our federalism doing it job perfectly..
if u r innocent u look only on the surface u think all victimhood is the same but they r not the same look under Amhara rule all the victim asked for break away state or statehood but under TPLF all victim only asking to be zone or state.. u see the big difference
under Amhara rule we had 100 freedom fighter or liberation front under federalism all the demand was to be zone or regional state.. now think about it when Federalism implemented correctly everyone will mind their own business and leave each other alone ... and we will live every happy
Re: ትኩረት ያላገኘው የአፋር ወጣቶች የመብት ትግል እና የሚደርስባቸው አፈና
Posted: 20 Apr 2019, 14:21
by Revelations
ትኩረት ያላገኘው የአፋር ወጣቶች የመብት ትግል እና የሚደርስባቸው አፈና
የአፋር ወጣቶች የመብት ትግል ቢያንስ ባለፉት አንድ ዓመት ብልጭ ድርግም እያለ ቀጥሏል።የሚገባውን ያህል ትኩረት አላገኘም።ስለዚህም ዛሬም የመብት ትግል ላይ ናቸው ዛሬም አፈና አለባቸው ዛሬም ትኩረት ይሻሉ።የመብት ተሟጋቹ ያሬድ ሀይለማርያም ይህን ያንብቡ ሼር ያድርጉት
መንግስት በአፋር ክልል ነዋሪዎች እና ወጣቶች ላይ እየደረሰ ያለውን የመብት ጥሰት ሊያስቆም ይገባል!
ባለፉት ትቂት ቀናት ውስጥ የክልሉ ልዩ ኃይል በተለይም ሰሙሮቢ ወረዳ የሚገኙ እና በሰላማዊ መንገድ ሰልፍ ወተው የመብት ጥያቄ ባነሱ ወጣቶች ላይ የኃይል እርምጃ የወሰደ ሲሆን በትንሹ 100 የሚሆኑ ወጣቶ ታፍሰው ለእስር ተዳርገዋል። ከአካባብው እና የአፋር ሰብአዊ መብት ተሟጋች ከሆነው ከአቶ ገአስ Gaas Ahmed ለማወቅ እንደተቻለው ወጣቶቹ አሁንም አስከፊ በሆነ የእስር አያያዝ ላይ ይገኛሉ።
መንግስት በሰላማዊ መንገደ ሃሳባቸውን ሲገልጹ የታሰሩትን ወጣቶች እና የአጋባቢውን ነዋሪዎች ያለምንም ቅድመ ሁኔታ እንዲፈቱ እና የኃይል እርምጃ በወሰዱትም የጸጥታ ኃይሎች ላይ የእርምት እርምጃ መውሰድ ይኖርበታል።
ባለፉት ሳምንታት በተከታታይ እየታየ ያለው ዜጎች ሃሳባቸው በሰላማዊ መንገድ እንዳይገልጹ የማደናቀፍ፣ የኃይል እርምጃ መውሰድ እና ማሰር ዜጎችን ለበለጠ አለመረጋጋት እና ሁከት ሊዳርግ ስለሚችል መንግስት እነዚህን ኩዳዮች በጥንቃቄ ሊከታተል እና ለጸጥታ ኃይሉም ሃሳባቸውን በሰላማዊ መንገድ በሚገልጹ በዜጎች ላይ የኃይል እርምጃ ከመውሰድ እንዲቆጠቁ ጥብቅ መመሪያ መስጠት ይኖርበታል።
ለአፋር ወጣቶች ድምጻችንን እናሰማ!
ያሬድ ሀይለማርያም
