Ejersa wrote: ↑16 Sep 2020, 21:36
በስነ ልቦና ምሁራን አገላለጽ መሰረት የበታችነት ስሜት ማለት ስለራስ ማንነት፣ ብቃት፣ ችሎታ ወይም በሌሎች የህይወት ገጽታዎች ከሌሎች ሰዎች በታች እንደሆኑ ማሰብና ስሜቱንም መለማመድ ነው፡፡ ይህ ከሌሎች በታች እንደሆኑ ማሰብ በትክክለኛ መረጃ ላይ የተመሠረተ ሳይሆን በተለያዩ አሉታዊ ጫናዎች የተፈጠረ አስተሳሰብና ስሜት ነው፡፡ የበታችነት ስሜት ለራስ ዋጋ አለመስጠት፣ ስለራስ ብቃትና ችሎታ መጠራጠር እንዲሁም በማንኛውም መለኪያ ከሌሎች ሰዎች ጋር እኩል እንዳልሆኑ ተቀብሎ መኖር ነው፡፡
ለበታችነት ስሜት ዕድገት አስተዋጽኦ የሚያደርጉ በርካታ ምክንያቶች አሉ፡፡ ከእነዚህ መካከል ዋና ዋና የሆኑት፣ ክፉ የአስተዳደግ ሁኔታ፣ የስነ–ልቦና ጥቃት ሰለባ መሆን፣ በተደጋጋሚ ችላ መባልና ያለመሳካት መደጋገም ናቸው።
የበታችነት ስሜት በቀላሉ ሊታይ የማይገባዉ አደገኛ በሽታ ነዉ። በዚህ በሽታ የተጠቁ ሰዎች በመጀመርያ ራሳቸዉን ይጠላሉ፤ ይህን ግን ለሌሎች አይገልፁም ይልቁንም የበሽታው ምልክት ሆኖ የሚወጣዉ የሌሎችን ሰብዕና ማራከስ ይሆናል ምክንያቱም የራሳቸዉን ሰብዕና ስለማይወዱ የሌላዉ መራከስ ለነሱ መጾናኛ ይሆናልና ነዉ። ዛሬ ዛሬ ሆሮሞዉን ጠባብ፣ አማራዉን ትምክተኛ እያሉ የሚያጥላሉት ወደዉና ፈልገዉ ሳይሆን በበታችነታቸዉ ስሜት ተገደዉ ነው።
የስነ ልቦና ምሁር የሆነው አልፍሬድ አልደር የበታችነት ስሜት ሰዎችን በጣሙን ጨካኝ እንደሚያደርግ ገልጿል (እዚህ ጋ የወያኔን ጭካኔ ልብ ይሉሃል)። ሌላዉ የበታችነት ምልክት ሌላዉን መወንጀል ነዉ። ሌሎችም እርስ በርሳቸዉ ሲወነጃጀሉ መመልከት የበታችነት ስሜት ለሚያሰቃያቸዉ ሰዎች ደስታን ይሰጣል፤ ምክንያቱም የሌሎች መራበሽ የራሳቸዉን ስሜት በጥቂቱም ቢሆን ይረሱ ዘንድ ከማድረጉም በላይ የአስታራቂነትን ቦታ በመቆናጠጥ የበላይ መስሎ በመታየት የዉስጣቸውን የትንሽነት ስሜት ሊደብቁ ይሞክሩበታል።
የበታችነት ስሜት መቼም የማይድኑት የተበድያለሁ ስሜትን ይቀብራል። ሌሎች ሊያጠፉኝ ነዉ የሚልን የሌለ ወይም የተጋነነ የተበዳይነትን ስሜት ያሳዝላል። በዚህ በሽታ የተያዙ ማህበረሰብ ወይም ግለሰቦች ለዉድቀታቸዉ መንስሄ ሁሌም ሌላዉን ያደርጋሉ። ዛሬ ዛሬ ወያኔዎች አማራዉ ታሪካዊ ጠላታቸዉ መሆኑን የሚገልፁት ወደዉ ሳይሆን በዚህ ምክንያት ነዉ።
ታዋቂዉ የስነ ልቦና ሙሁሩ ኤሪክ ኤሪክሰን ይህን የወያኔን መሰሉን የበታችነት ስሜት መለማመድ ሲያብራራ “During the elementary school stage (ages 6–12), children face the task of industry vs. inferiority. Children begin to compare themselves with their peers to see how they measure up. They either develop a sense of pride and accomplishment in their schoolwork, sports, social activities, and family life, or they feel inferior and inadequate because they feel that they don’t measure up. If children do not learn to get along with others or have negative experiences at home or with peers, an inferiority complex might develop into adulthood.” ወያኔ ያሳደጋቸው የትግሬ ሕጻናት ከልጅነታቸዉ ጀምሮ ይህን የበታችነት ስሜት ሲቀለቡ ያድጉና ሲጎረምሱ የለየላቸዉ ተጠራጣሪዎች ቢወጣቸዉ እንዴት ይገርማል።
የበታችነት ስሜት ሌላዉ መገለጫዉ ደግሞ ምንም አይነት ተግሳጽን ለማስተናገድ አለመቻል ነዉ (sensisivity to criticism)። ወያኔ የኢትዮጲያን ሕዝብ በምንም ሁኔታና በምንም ጉዳይ ይቅርታ ጠይቆ የማያውቅበት ምክንያት የዚህ የበታችነት ስሜት ዉጤት ነዉ።
ብዙዉን ጊዜ የበታችነት ስሜት በሽታ ያለባቸዉ ሰዎች፤ ዉሃ ተጠምተው ሳላ ጥማቸዉን ለማርካት ዉሃ ከመጠጣት ይልቅ እንጀራ የሚያግበሰብሱ በመሆኑ ከበሽታቸዉ ጋር በማመሻሸት ለራሳቸዉም ለሀገርም ችግር ሲሆኑ ይታይሉ።
በበታችነት ስሜት የሚንገላቱት ወያኔዎች፤ ተማሩ ይባሉ ዘንድ ዲፕሎማ ቢሸምቱ፣ ባለ ስልጣን ይባሉ ዘንድ የአገሪቷን ስልጣን ከሀ እስከ ፐ ቢቆጣጠሩ፤ ጀግና ይባሉ ዘንድ በአገሪቷ ታሪክ ለመጀመሪያ ጊዜ ባለ ሙሉ ጀነራልነት ማእረግ አንድም የጦር ት/ ቤት እግሩ ረግጦ ለማያዉቀዉ የመንደራቸዉ ሰዉ ቢሰጡ፤ የመንፈሳዊያንን ቦታ እንኮ በቀድሞ ፓትሪያርክ ለተወገዙ የቀበሌያቸዉ ሰዉ ቢሰጡ፤ ሀብታም የሆኑ ይመስላቸዉ ዘንድ ችርቻሮ ንግዱን እንኯ ሳይቀር ቢቆጣጠሩ ጥማቸው መቼም ሊረካ አይችልም። በራሱ የሚተማመንና ሙሉ ሰዉ የሚያደርግ የእዉቀት ዉኃ ተጠምተዉ፣ እነሱ ግን ሌት ተቀን ተራ ቁሳቁስን በመሰብሰብ ራሳቸዉን በበታችነት ቁንጣን ያስጨንቃሉ። በርካቶቹም እንደተጨነቁ ያልፋሉ።