Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Hameddibewoyane
- Member
- Posts: 3890
- Joined: 25 Sep 2019, 02:42
Post
by Hameddibewoyane » 09 Jan 2020, 10:32
"ህወሃት እያካሄደ ባለው የሴራ ፖለቲካ ላለመሳተፍ ከፌዴራሊስት ሃይሎች ፎረምና ምክትል ሊቀ መንበርነቴ እራሴን አግልያለሁ" ሲሉ አቶ ትዕግስቱ አወል አስታወቁ።
የአንድነት ለፍትህና ለዴሞክራሲ ሊቀ መንበር አቶ ትዕግስቱ አወሉ በህወሃት ጋባዥነት ትግራይ ክልል ሄደው የፌዴራሊስት ሃይሎች ፎረም በመመስረት በምክትል ሊቀመንበርነት መመረጣቸውን ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቃለ መጠይቅ ገልጸዋል።
ዛሬ ከሃላፊነታቸውና ከፎረሙ ራሳቸውን ማግለላቸውን ያስታወቁት አቶ ትዕግስቱ፤ ግብዣው በተደረገበት ወቅትና ፎረሙ ሲመሰረት ዋና አላማ ያደረገው "ህገ መንግስቱ እየፈረሰ ስለሆነ እናድን ፌደራሊዝም ስርአቱም ወደ አሃዳዊነት እየተቀየረ ነው" በሚል መነሻ እንደነበረ አመልክተዋል።
ይሁን እንጂ ፌዴራሊስት ሃይሎች ፎረም ተብሎ እየተዋቀረ ያለው አደረጃጀት ፍፁም ዴሞክራሲያዊ ያልሆነና የቀድሞውን ያረጀ አስተሳሰብ ያነገበ መሆኑን በመረዳታቸው ከሃላፊነታቸውና ከፎረሙ መልቀቃቸውን አስታውቀዋል።
ህወሃት ያደራጀው የፌዴራሊስት ሃይሎች ፎረም ገና ህጋዊ እውቅና እና ሰነድ ያላገኛ ከመሆኑም በላይ ትግሉን ለማካሄድ የሚፈልግበት መንገድ "የሃይል እርምጃን ጨምሮ ማንኛውንም አማራጭ እጠቀማለሁ የሚል ነው" ሲሉም ተናግረዋል።
በመሆኑም "ይህ አካሄድ ቢመቻቸው እነርሱ የሚፈልጉት ብሄር ተኮር የሴራ ፌዴራሊዝም ካልተቻለ ደግሞ የመነጠል ፖለቲካ ይዘው መንቀሳቀስ ነው" ብለዋል።
ይህ አካሄድ "የትግራይን ህዝብ ጨምሮ የኢትዮጵያ ህዝብ ዳግም ሊያስለቅስ የተነሳ ነው" ያሉት አቶ ትዕግስቱ፤ አሁን እየተካሄደ ያለውን ለውጥ "አሃዳዊ ነው ብለው የፈረጁት ህዝቡን ለማነሳሳት የተጠቀሙበት ሴራ ነው" ሲሉ ገልጸውታል።
በመሆኑም የአንድነት ፓርቲ አሁን እየተተገበረ ካለው ፖለቲካዊ ለውጥ ጎን "በዴሞክራሲያዊ መንገድ ለአገርና ለህዝብ የሚጠቅም ፖለቲካ እሳተፋለሁ እንጂ ይህን የሴራ ፖለቲካ ልከተልም አልችልም" ሲሉም ተናግረዋል።

-
Ejersa
- Member
- Posts: 3978
- Joined: 05 Nov 2019, 10:39
Post
by Ejersa » 09 Jan 2020, 10:47
በገና ማግስት ለህወሓት ይሄ ትልቅ መርዶ ነው

-
Hameddibewoyane
- Member
- Posts: 3890
- Joined: 25 Sep 2019, 02:42
Post
by Hameddibewoyane » 09 Jan 2020, 10:56
ጉድ ሰራቸው !! ትህነጎች አለ የተባለውን የጥፋት ፖለቲካ ሞክሩ አልተሳካላቸውም ። አሁን የቀራቸው አንድ ዕድል ብቻ ነው ። ገመድ ገዝቶ መታነቅ ፤ ከዛ mission accomplished!!
Ejersa wrote: ↑09 Jan 2020, 10:47
በገና ማግስት ለህወሓት ይሄ ትልቅ መርዶ ነው
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4486
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40
Post
by Za-Ilmaknun » 09 Jan 2020, 11:23
I am waiting for Ayele Chamiso to openly come out and make such a statement

. All those sellouts will do same once they see carrot hanging in front of them. They are only in the so called TPLF camp to mooch every penny they could from the bloodsuckers.
-
Za-Ilmaknun
- Member
- Posts: 4486
- Joined: 15 Jun 2018, 17:40
Post
by Za-Ilmaknun » 09 Jan 2020, 12:44
Ejersa wrote: ↑09 Jan 2020, 12:38
Woyane is officially dead & we need to know the date of the funeral from the digital woyanes
Za-Ilmaknun wrote: ↑09 Jan 2020, 11:23
I am waiting for Ayele Chamiso to openly come out and make such a statement

. All those sellouts will do same once they see carrot hanging in front of them. They are only in the so called TPLF camp to mooch every penny they could from the bloodsuckers.
That group has been dead ever since it officially declared the people of the country as its enemies. It fasten its death when it started selling the sovereignty of the country left and right in exchange for small favors from Sudan. It is a renegade group that probably is the first of its kind in the world where acting as a government, actively working to dismember its own country. It was a group that captured the state and abused it to the max it could for 30 years. No amount of anything could save such barbarism and greed.

-
Hameddibewoyane
- Member
- Posts: 3890
- Joined: 25 Sep 2019, 02:42
Post
by Hameddibewoyane » 09 Jan 2020, 13:06
ወዳጄ ትእግስቱ አወሉ ህወሓትን በመተዉ አትገረም። ገና የህወሓት ባለስልጣናት ማሩን ብልፅግና" እያሉ። ከትግራይ ወደ አዲስ አበባ ምክንያት ፈጥረው በመምጣት እጃቸውን ይሰጣሉ።