Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
MINILIK SALSAWI
Senior Member
Posts: 11059
Joined: 24 Aug 2012, 12:02
Contact:

ከፍተኛ ትችትና ተቃውሞ ያጋጠመው የኢትዮጵያ ታሪክ መማሪያ ሞጁል ላይ ምሁራን ከስምምነት ሊደርሱ አልቻሉም።

Post by MINILIK SALSAWI » 27 Dec 2019, 09:35

አደገኛውና ሕዝብን የሚያጋጨው ሌላ ቁስል የሚፈጥር ቁስሉን በመነካካት ሌላ ቁርሾ የሚሻ የኢትዮጵያ ታሪክ መማሪያ ሞጁል ባሕልን፣ እምነትን፣ የዜግነት ግዴታና የሙያ ክብር ያላገናዘበና ያላከበረ በተወሰኑ ሕዝቦች ላይ ያነጣጠረ ጥላቻ የተሞላበት መሆኑ ምሁራን ይናገራሉ።

በሃሰት ታሪክ እና በሞያው እውቀት በሌላቸው ካድሬዎች የተዘጋጅ ነው:: የፈጠራ ታሪክን ጥላቻ የተሞላበት የታሪክ ማስረጃ የሌላቸውን ታሪኮች ለከፍተኛ ትምሕርት ተቋማት መማሪያነት ማዘጋጀት ወንጀል ነው።ሌላ ቁስል የሚፈጥር ወይም ቁስሉን በመነካካት ሌላ ቁርሾ የሚሻ የትናንቱን ጉዳት በእርቅና በይቅርታ ከማስቀረት ይልቅ የበለጠ ጥርስ መነካከስን የሚያበረታታ ባለመስማማትና በትችት የተበተነውን ውይይት በስምምነት ጸደቀ የሚል ሰፊ ፕሮፓጋንዳ መንግስት ሊሰራበት ተዘጋጅቷል።

አዲሱ የታሪክ ትምህርት የማስተማሪያ ሞጁል/ሰነድ የኃላ ቁስልን ያልተወ፣ የሚያጋጭ ፣ መልካም የታሪክ ጎንን የማያስተምር ፣ ለፖለቲካ አጀንዳና የግለሰቦችን ፍላጎት የተጻፈ ፣ ሚዛናዊነት የጎደለው፣ ታሪክን ለ አገር ግንባታ ለመጠቀም ያልፈለገ፣ አብሮነትን የጨፈለቀ ፣ ትውልድን የማያፈራ ፣ ከታሪክ እየተማረ ጠንካራ አገር መፍጠር የማያስችል ወዘተ የሚል ትችት በምሁራን ተሰንዝሮበታል። ባሕልን፣ እምነትን፣ የዜግነት ግዴታና የሙያ ክብር ያላገናዘበና ያላከበረ በተወሰኑ ሕዝቦች ላይ ያነጣጠረ ጥላቻ የተሞላበት መሆኑ ምሁራን ይናገራሉ።#MinilikSalsawi