አዲስ አበባ፣ ታህሳስ 15፣ 2012 (ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ለብልጽግና ፓርቲ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጠው ውሳኔ አሳለፈ።
የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ በፓርቲዎች ምዝገባ ጥያቄዎች ዙሪያ የተለያዩ ውሳኔዎችን በዛሬው እለት አሳልፏል።
ቦርዱ የእውቅና ጥያቄ እና የፓርቲ መለያ ሰንደቅ አላማ የማጸደቅ ጥያቄን ያቀረቡ ፓርቲዎችን ጉዳይ በመመልከት ውሳኔ ማሳለፉንም ነው ዛሬ የገለፀው።
የኢህአዴግ አባል የነበሩ ሶስት ፓርቲዎች እና ሌሎች አምስት ፓርቲዎች በጋራ ራሳቸውን በማክሰም ብልጽግና ፓርቲን መመስረታቸውን በማሳወቅ የእውቅና ሰርተፍኬት እንዲሰጣቸው ህዳር 24 ቀን 2012 ዓ.ም ጥያቄ ማቅረባቸውን ቦርድ አስታውሷል።
https://www.fanabc.com/%e1%88%9d%e1%88% ... %e1%88%b0/