ዓረና ከህዝብ በይፋ እውቅና ባገኘበት ጊዜም ህወሓቶች ከአራት በላይ የዓረና አባላትን ገድለዋል፣ በትግሉ ጊዜ አመርቂ ተሳትፎ የነበራቸውም ታስረዋል። ዛሬ ደግሞ ህወሓት ተሸንፋ ትግራይ በተደበቀችበት ወቅት የዓረና አመራሮችን ለመግደል ሞክራለች፣ የህወሓት ታጋይ ነበር የዓረናው የአመራር አባል ሃይለኪሮስ ታፈረ፣ ብዙ ጊዜ ታስረዋል፣ ይሰራበት ከነበረ የንግድ እንቅስቃሴም በተዘዋዋሪ እንዲያቆም አድርገውታል፣ አሁን የውቅሮ ህዝብ ህወሓትን በጠላበት ጊዜ፣ የዓረና የበላይነት እና የህወሓትን የበታችነት ምንጩ ሃይለኪሮስ ታፈረ ነው ያሉት ህወሓቶች፣ በመርዝ ለመግደል ሞርከው አልተሳካላቸውም፣ ዛሬ ሃይለኪሮስ ህክምና እርዳታ ተደርጎለት ሊተርፍ ችለዋል። ሃይለኪሮስ ታፈረ 1983 ታንክ ይዘው አዲስ አበባ ከገቡ የህወሓት ታጋዮች አንዱ ነው።
የህወሓቱ ታጋይ እና የጥበብ ሰው እያሱ በርሀ፣ በህወሓት አመራሮች በመርዝ ተመርዞ እንደሞተ ሚስጥር አይደለም፣ ከህወሓት ውድቀት ቦሃላም ለትግራይ ህዝብ ይተረክለታል፣ እያሱ በርሀ በመርዝ ሲገደል ዝምታን የመረጠ የትግራይ ሙሁር ሃይለኪሮስ ተመርዞ ቢገደል ኖሮም ምርጫው ዝምታ ነው።፣አርቲስት እያሱ በረሀ ያኔ ዉሃ ጠጥቶ ነው የሞተው ብለውናል።.ልክ ጀነራላ በርሀ ሻዕብያ ሚስቱ በቅናት ነው የገደለችው እንዳሉን ማለት ነው።
. ትናንት በዶ/ር አረጋዊ በርሀ እና በሹፌሩ ላይ የሞከሩት አልተሳካላቸውም፣ ዛሬም በሃይለኪሮስ የሞከሩት ግድያም አልተሳካላቸውም። የዓረና ትግራይ ዝናቡ በህወሓት ደህንነቶች ተመርዞ መሞቱ ሳንረሳ ጊዜ ለኩሉ ብለናል ፣የአቶ አስገደ ገብረስላሴ የልጃቸው ባልም መርዝ አስተጥተው ገደል ላይ ወርውረዉታል። ያቺ ቀን ትመጣለች፣ ያኔ ሂሳብ ይወራረዳል!!! የህወሓት አመራሮች እናንተ በሰራቹት ግፍ ለልጆቻቹ እንዳይተርፍ!!!

