Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum

sholagebya
Member
Posts: 494
Joined: 27 Oct 2014, 15:59

Re: Yalsema Yisma: ''አብይን አውቀዋለሁ፣ሥርዓቱን እንደሚያፈርሰው አውቃለሁ'' ጃዋር መሐመድ ETHIO FORUM

Post by sholagebya » 14 Dec 2019, 14:55

ሠርጉን ተዝካር ትለዋለህ አሉ :: “ የብልጽግና ፓርቲ ምርጫውን ካሸነፈ የጎሳ ፌዴራሊያዊ ስርአቱን ያፈርሰዋል ! “ ይህ እንግዲህ የእነ ወያኔና የጃዋር ግንባር የሚፈበርከው ፕሮፓጋንዳ ነው :: ይህን ጠቅላይ ሚኒስትር አብይ ሆነ የብልጽግና ፓርቲ እንደ ግንባር ወይም ድርጅት የሚያምንበት እንዳልሆነ እናውቃለን :: የዚህ ቅስቀሳ አላማ ምን እንደሆነ ጠንቅቀን እናውቃለን :: የብሔርና ብሔረሰቦች ወይም ደግሞ ራሳቸውን በጎሳዊ ድርጅት ያደራጁ ኃይሎችን በጸረ-የብልጽግና ፓርቲና በጸረ-አብይ አመራር ለማሰለፍ ሲባል ነው :: በርግጥ የጎሳ ፌዴራሊዝም መፍረስ , ሁሉም ኢትዮጵያዊ በሕግ ፊት በእኩልነት የሚታይበት ስርአትና , የግለሰብ ነጻነት የተከበረባት ኢትዮጵያን መመስረት የአንድነት ኃይሎች የሚመኙት ይሆናል :: ይህ የሚሆነው በሁሉም የኢትዮጵያ “ ሕዝቦች “ ፍላጎት እንጂ በብልጽግና ፓርቲ ብቸኛ ውሳኔ አይደለም :: ብሔርና ብሔረሰቦች ወይም ደግሞ እራሳቸውን በጎሳ ያደራጁ ኃይሎች በሙሉ መብታችን እንደ ዜጋ እንደሚከበርልን እናምናለን ብለው ሲወስኑ ብቻ ይሆናል :: ስለዚህ የብልጽግና ፓርቲ ሆነ የጠቅላይ ሚኒስትር አብይ አህመድ አመራር የፌዴራል ስርአቱን ሊጨፈልቅ እንደማይችል የታወቀ ነው :: ይህቺ ቅስቀሳ ያለ ምንም ጥርጥር የወያኔ/ኦነግና ጃዋር የማታጋያና የውዥንብር የፈጠራ ታክቲክ ነች :: የእነዚህን እኩይ አላማ ለማክሸፍ የኢትዮጵያ ሕዝብ ከብልጽግና ፓርቲና ከአብይ ጎን መሰለፍ ያለበት ጊዜ አሁን ነው :: እንጂ እማ የጎሳን ፌዴራሊዝምን በመጨረሻ ማጥፋትና ማክሰም የኢትዮጵያዊነት የረጅም ጊዜ እስራቴጂካዊ ስኬት ነው :: ይህ የሚሆነው ግን በኃይል በመጫን እንደማይሆን ሁላችንም እናውቃለን :: << አብይን አውቀዋለሁ >> ውሸታም ቱሩናፋ ... ለዚያች ሞኝ አማትህ ንገራት ታምንክ ከሆነ ::
የብሔርና የብሔረሰብ ወይም የጎሳ ድርጅቶች በጣም የተሻለ አማራጭ የሚሆናቸው , ይህን የወያኔ የውሸት ፕሮፓጋንዳ ከማመና ከወያኔ ጎን ከመሰለፍ ይልቅ , አሁን ባለው ሕጋዊ ፍሬም ወርክ ከአብይና ከብልጽግና ፓርቲ ጋር በመሰለፍ የሕዝባቸውን መብት ማስከበር ይሆናል ::
አለበለዚያ ቀብራችሁን ከወያኔ ጋር ማፋጠን ይሆናል :: Who would have thought ወያኔ would be dismantled from within ? No body !!



Halafi Mengedi wrote:
14 Dec 2019, 12:10

Sam Ebalalehu
Member
Posts: 3639
Joined: 23 Jun 2018, 21:29

Re: Yalsema Yisma: ''አብይን አውቀዋለሁ፣ሥርዓቱን እንደሚያፈርሰው አውቃለሁ'' ጃዋር መሐመድ ETHIO FORUM

Post by Sam Ebalalehu » 14 Dec 2019, 16:54

Halafi, is not strange that Jawar is “sweating” because Abiy is planning to disintegrate Ethiopia? Indeed.

Post Reply