+ ህውሃት አገሪቱን በክልል ከፋፍሎ ሲሻው አጣምሮ ሊገዛ፤ ሳይፈልግ ሲቀር ደግሞ ሊያፈርሳት በሚያመቸው መንገድ ያዋቀራትን ኢትዮጵያን ለመታደግ ለሚታገሉ ኃይሎች ትልቅ አቅም ይፈጥራል፤
+ ቋንቋን መሰረት አድርገው የተካለሉት ክልሎች እያደር አገር ወደመሆን የጀመሩትን የቁልቁለት ጉዞ በተወሰነ ደረጃም ቢሆን ለማክሸፍ ይቻላል፤ በከፊል ያልኩት የዛሬዋ ኢትዮጵያ በሙሉ ቅርጿ ትቀጥላለች ወይ የሚለውን መቶ በመቶ እርግጠኛ ሆኖ መናገር ስለማይቻል ነው፤
+ ዶ/ር አብይ ከታሰሩበት የፓርቲ ወጥመድ በተወሰነ ደረጃ ነጻ የመሆን እድል ይፈጥርላቸዋል። አብይ በዛሬው አቋሙ የኦዴፓ እስረኛ መሆኑን አፍ ሞልቶ መናገር ይቻላል። እርምጃውም ሆነ ንግግሩ ኦዴፓ በፈቀደለት ልክ መሆኑን በሰሞኑ ክስተቶች በደንብ አሳይቷል። ጠቅላይ ሚኒስትር ሆኖ የመቀጠል እድሉም በኦዴፓ እጅ ነው ያለው። ስለዚህ ይህ ውህድ ፓርቲ አብይን ከእስር ነጻ ያወጣዋል የሚል ግምት አለኝ።
+ የአብይ ከኦዴፓ እስር ነጻ መውጣት ደግሞ በሙሉ አቅሙ በአገሪቱ ውስጥ ሕግ እና ሥርዓትን ለማስከበር አቅም ይፈጥርለታል።
+ አብይ ሕግ ማስከበር ከጀመረ ኢትዮጵያ እንደ ጃዋር ያሉ ጽንፈኛ ፖለቲከኞች የሚፈነጩባት እና ከሕግ በላይ ሆነው ያሻቸውን የሚያደርጉባት አገር መሆኗ ያበቃ ይሆናል።
+ ውህዱ እውን ሲሆን ከአራቱ ድርጅቶች ውጭ የነበሩ አጋር ድርጅቶች እና ሌሎች ኃይሎችም በአብይ ዙሪያ በመሰባሰብ አቅም ስለሚፈጥሩለት በራሱ ድርጅት በኦዴፓ ውስጥ የሚገዳደሩትን አክራሪ ኃይሎች አሸንፎ መውጣት ይችላል፤
+ ህውሃት ውህዱን ስካልተቀላቀለች ድረስ በህውሃት እና በፌደራል መንግስቱ መካከል ያለው ግንኙነት ግልጽ መልክ ይይዛል። ሕውሃት የገዢ ፓርቲ አካል ሳትሆን ተቃዋሚ ሆና ትቀጥላለች። ይህ አይነቱ አሰላለፍ ከምርጫው በፊት የአገሪቱን በተለይም ትግራይን የማስተዳደሩ ጉዳይ ላይ ሌላ ውዥንበር ቢፈጥርም ለመፍትሔ ግን በር ሊከፍት ይችላል።
+ አዲሱ ውህድ ፓርቲ በአንዳንድ ክልሎች ድጋፍ ቢያጣ እንኳ በምርጫው ስልጣን እንዳያጣ እንደ ኢዜማ ካሉ ህብረ ብሄራዊ ድርጅቶች ጋር እስከ መዋሃድ ሊሄድ ይችላል።
+ አዲሱ ውህድ እና ኢዜማ ግንባር ፈጥረው ከተዋሃዱ በብሄር ተደራጅተው ከሕውሃት ጎን የሚቆሙትን ኃይሎች ለመገዳደር አቅም ይፈጥርላቸዋል።
ፀሃፊ፦ Yared Hailemariam
ሙሉ ፅሁፉን ለማንበብ ከታች ያለውን ሊንክ/ምስል ይጫኑ
https://ethiothinkthank.com/2019/11/13/ ... NdOCZWdc5Q