Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
Hameddibewoyane
Member
Posts: 3890
Joined: 25 Sep 2019, 02:42

ታሪክ አይዋሽም!

Post by Hameddibewoyane » 15 Oct 2019, 09:49

የወልቃይት፣የጠገዴ፣የካፍታ ሁመራና የጠለምት ህዝብ ጎንደሬ አማራ ኢትዮጵያዊ ነዉ።የትግራይ ኤሊቶች ወልቃይት የወልቃይት ነዉ በወልቃይት ጉዳይ የሚያገባዉ ወልቃይቴዉ ብቻ ነዉ የሚል ነጠላ ዜማ ለቀዋል።ወልቃይት ወልቃይት ነዉ፤ዋግ ዋግ ነዉ፣ራያ ራያ ነዉ፣ተምቤን ተምቤን ነዉ፣እንደርታ እንደርታ ነዉ ነገር ግን ከታሪክ አንፃር አንድ እዉነት አለ ወልቃይት ጎንደር ነዉ፤ዋግ ወሎ ነዉ፤ራያ ወሎ ነዉ፤ተምቤን ትግራይ ነዉ፤እንደርታ ትግራይ ነዉ።

መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚያዉቀዉ የወልቃይት ጠገዴ መሬት የጎንደር አካል ነዉ ስለዚህ የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም ጎንደሬ ጉዳይ ነው።ወልቃይት ጠገዴ መሬቱም ህዝቡም አማራ ነው ስለዚህ የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም አማራ ጉዳይ ነዉ። የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከመላዉ የጎንደር ህዝብ ጋር በደም የተሳሰረ ዝምድና አለዉ።የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ የሚሉት የወልቃይት ህዝብ ከጎንደር ህዝብ ጋር ያለዉን የዘር ሀረግ ትስስር ለመበጠስና ወልቃይትን እንደ ፈለጉ ለመቆጣጠር እንድያመቻቸዉ ነዉ። የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ እያሉ የሚያዜሙት የወልቃይትን ህዝብ ከጎንደር ህዝብ ለመለየት የሚያደርጉት የስነ ልቦና ፕሮፓጋንዳ ነዉ።የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ እያሉ የሚለፍፉት ወልቃይትን ከጎንደር በመነጠል የጎንደር ክፍለ ሀገርን የግዛት አንድነት ለማፈራረስ ነዉ።

ወልቃይት የጎንደር አካል ነች!
የወልቃይት ጉዳይ የመላዉ አማራ ጉዳይ ነዉ።

Hameddibewoyane
Member
Posts: 3890
Joined: 25 Sep 2019, 02:42

Re: ታሪክ አይዋሽም!

Post by Hameddibewoyane » 15 Oct 2019, 10:15

የኢትዮጵያ መንግስት (ኢ.ህ.አ.ዴ.ግ) አዲስ አበባን ከተቆጣጠረ በኋላ ከወሰዳቸው ዓብይ ኩነታት አንዱ፤ የሀገሪቱን የፖለቲካን የአስተዳደር ካርታን መቀየሩ እንደሆነ ይታወቃል:: የኢትዮጵያ ክፍላተ ሀገራት ካርታ እ.ኤ.አ. በ1994 ቢቀየርም፤ አዲሱ ካርታ ብዙ የማንነት ጥያቄዎችን አስነስቷል:: ይህ የዳግም መካለል ጥያቄ ከሚነሳባቸው ቦታዎች ውስጥ ወልቃይት አንዱ ነው።

እንዲህ አይነት የማንነትና የመካለል ጥያቄ ሲቀርብ ዋና መፍትሄ የሚሆኑት የታሪክ ሰነዶች ናቸው:: የታሪክ ሰነዶች ስለ ወልቃይት ግን ምን ይላሉ? ላለፉት ብዙ መቶ ዓመታት የተጻፉ የታሪክ ሰነዶች ምን እንደሚሉ እንመርምር::

ወልቃይት ጠገዴና አላማጣ ኮረም በአጼ ዮሓንስ ዘመን በትግራይ ሥር አልነበሩም –የታሪክ ሰነድ ማስረጃ

አጼ ዮሓንስ ከ 1871 ዓ.ም እስከ 1889ዓ.ም (እ.ኤ.ኣ) ኢትዮጵያን የመሩ ንጉስ ናቸው:: ንጉሰ በንግሥና ዘመናቸው የራሳቸው ጠንካራና ደካማ ጎን ቢኖራቸውም፣ ከጠላት ደርቡሽ ጋር በመፋለም ለሀገራቸው ክቡር ሕይወታቸውን የሰጡ ንጉሰ ናቸው:: ጥቂት የማይባሉ የሕወሀት ሰዎች፣ ከወልቃይትና ጠገዴ ጋር በተያያዘም የሚጠቅሱት እሳቸውን ነው:: “ወልቃይት እና ጠገዴ ፣ ጥንት በአጼ ዮሓንስ ዘመነ መንስግት በትግራይ ስር ነበረች”በማለት እንደ ዋና መከራከርያ ሲያቀርቡት ይደመጣል:: እውነታውን የዘገቡት የታሪክ ሰነዶች ናቸውና የታሪክ ሰነዶችን እንመርምር::

በአጼ ዮሓንስ ዘመን የነበረው የትግራይ ግዛትና፣ አጠቃላዩ የኢትዮጵያ ግዛት ምን እንደሚመስል በዝርዝር በሀገር ውስጥና በውጭ ሊቃውንት ተጽፏል:: ስለ ወልቃይትም አስተዳደር በማን ስር እንደነበረ በዝርዝር ጽፈውታል:: ለዚህም የእውቁን የፈረንሳዊ የጂኦግራፊ ፕሮፌሰር ኤሊስ ሬክለስ መጽሓፍን በዋቢነት መጥቀስ ይቻላል::

በዩንቨርሲቲ ኦፍ ብረስልስ የኮምፓራቲቭ ጂኦግራፊ (University of Brussels, Professor of Comparative Geography) ፕሮፌሰርና የዴፓርትመንቱ ሀላፊ የነበረው ይሄው ፕሮፌሰር ፤ በ1880 ጀምሮ በርካታ መጽሓፎችን በዓለም ጂኦግራፊ ላይ ጽፏል:: እነዚህም መጽሓፍቱ ከለንደንና ፓሪስ ጆኦግራፊካል ሶሳይቲ የወርቅ ሜዳሊያ ተሸላሚ አድርገውታል::

ከነዚህ መጻሕፍት አንዱ በ 1880 የተጻፈው The Earth and its Inhabitants የሚለው ሲሆን፤ ዘጠኝ ተከታታይ ክፍሎች አሉት። የዚሁ መጽሓፍ ክፍል አራት በገጽ 443 ላይ የሰሜን እና ምስራቅ አፍሪካን የወቅቱን ጂኦግራፊ በዝርዝር ይተነትናል:: በአጼ ዮሓንስ ዘመን የነበረውንም የኢትዮጵያን ክፍላተ ሀገራት በዝርዝር ቁልጭ አድርጎ እንዲህ ጽፎታል::

“The Amhara government provinces are: Dembia, Chelga, Yantangera, Dagossa, Kuarra, Begemidir, Guna, Saint, Wadla, Delanta, Woggera, Simen, Tselemt, Armachiho,Tsegede, Kolla Wogerra፣ Waldiba and Wolkait”

ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርኩት ይህ ጽሁፍ የተጻፈው በ1880ዎቹ አጼ ዮሃንስ የሀገሪቱ ንጉስ በነበሩበት ዘመንና የተጻፈውም በግዜው ከነበሩ ከተለያዩ የጂኦግራፊካል ሶሳይቲዎች የወርቅ ሜዳይ ተሸላሚ በሆነ ባለሙያ ፕሮፌሰር ነው:: ይህ በ1880ዎቹ የተጻፈው መጽሓፍ እንደሚያስረዳው በአጼ ዮሓንስ ዘመን ወልቃይት: ጠለምት : ዋልድባ : አላማጣ : በሙሉ በትግራይ ስር አልነበሩም:: እነዚህን ቦታዎች በስም ጠቅሶ እንደሚነግረን በትግራይ ስር ሳይሆን በጎንደር ስር ነበሩ::



በኣጼ ቴዎድሮስም ዘመን ወልቃይት ጠገዴ በትግራይ ስር አልነበሩም – የታሪክ ማስረጃ ሰነዶች

በኣጼ ቴዎድሮስ (1818 – 1868 እ.ኤ.አ) የነበሩ ስመ ገናና ኢትዮጵያዊ ንጉስ ነበሩ:: በየቦታው የነበሩ መሳፍንትን አሸንፈው፣ ማዕላዊ መንግስት ከመሰረቱ በኋላ፣ ቀጣይ ራዕያቸው የምዕራብያውያንን ቴክኖሎጂ እዚሁ ኢትዮጵያ እንዲመረት ማድረግ ነበር:: ለዚህም ከበርካታ አውሮፓ ሀገራት ጋር ግንኙነት መስርተው ነበር:: የአውሮፓውያን ጥበበኞችን ኢትዮጵያ ለማስቀረት እና ጥብቅ ግንኑነት ለመመስረት፣ አጼ ቴዎድሮስ ልጃቸውን ለአንድ ስዊስ ኢንጂነር እስከመዳር ደርሰው ነበር:: በዚህም ምክንያት በርካታ አውሮፓውያን ጠቢባን በአጼ ቴዎድሮስ ዘመን ኢትዮጵያ መጥተዋል:: እነዚህም ባለሙያዎች ኢትዮጵያ መጥተው ስለ ሀገሪቱ በዝርዝር ጽፈዋአል:: የእንግሊዝ መንግስትና የኢትዮጵያ ግንኑነት መሻከር ሲጀምር፣ እንግሊዞች ስለኢትዮጵያ ይበልጥ የማወቅ ፍላጎታቸው ጨመረ::

የእንግሊዝ መንግስት የintelligence ሰዎችም የእንግሊዝ መንግስት ፓርላማና የጸጥታው ኃይል ኢትዮጵያን በሚገባ ያውቃት ዘንድ ትዕዛዝ ወጣ:: የእንግሊዙ Topographical and Statistical Department of The War Office ኤ . ሲ ኩክ (A. C. Cook) በተባለ እንግሊዛዊ ኮሎነል አማኻኝነት ስለ ኢትዮጵያ ከ15ኛው ክፍለ ዘመን ጀመሮ በተለያዩ እውሮፓውያን ተጻፉ መጻሕፍት ባንድ ላይ እንዲጠርዘ ተደረገ:: የሚደንቀው ይሄ መጽሓፍ በ 1867 ዓ.ም እ.ኤ.ኣ የታተመው በግስቲቷ ጥያቄ ለእንግሊዝ ሀውስ ኦፍ ኮመን ሎወር ሀውስ ግብአት (House of Common lower House) ይውል ዘንድ መሆኑ ነው:: በዚሁ መጽሓፍ ውስጥ፤ የወቅቱ የኢትዮጵያ ዝርዝር ጉዳይ ተጽፏል:: ይሄውም መጽሓፍ ስለ ወልቃይትና ጠገዴም በኣጼ ቴዎድሮስም ይሁን ከሳቸው በፊት በማን ስር ይተዳደሩ እንደነበር በዝርዝር ያትታል::

“The Provinces of Amhara are : Simen, Waldibba, Wolkait,Wogera,Chilga, Kuara, Belesa, Fogerra, Damot, Gojjam, Begemidir, Beshilo ….. Waldiba situated to the NW of Semein between the Tekeze and the Angereb, extends as far as the junction of the two rivers. Welkait is to the west Of Waldiba it is intersected through its whole length by the two river tekuar and guang. It is more wooded than waldiba..” (Routes in Abyssinia (printed in 1867 G.C) page 188)

ይሄው ታሪካዊ መጽሓፍ በወቅቱ የነበረውንም የትግራይ ክፍለሀገር ድንበር እና ግዛት እነማን እንደነበሩ በማያሻማ ቋንቋ እንዲህ ይነግረናል፡፡

“The territory of Tigre whose capital is Adwa, is bounded on the West by Shire, on the Southwest by Temben and Adet on the South by Geralta on the South –East by Haramat, on the East by Agame, and on the North by the rivers of Mereb and Belessa”

የትግራይ ግዛትስ? ብሎ ለሚጠይቅ ወገን ፤ ይሄው መጽሓፍ በወቅቱ የነበርቸው ትግራይ ምን እንደምትመስል እንዲህ ሲል አስፍሮታል በዚሁ መጽሓፍ ላይ ገጽ 187 – 188 የትግራይን ግዛት እንዲህ ሲል ይገልጸዋል

“The territory of Tigray whose capital is Adwa is bounded on the west by Shire, on the south west by Temben and Adet, on the south by Geralta, on the South East by Haramat, on the East by Agamae, and on the North by the Rivers Mereb and Belessa”

እዚህ ላይ በ 18ተኛው ክፍለ ዘመን የትግራይን ወሰኖች በማያሻማ ሁኔታ በግልጽ አስቀምጦታል:: የትግራይ ወሰን በምዕራብ – ሽሬ ፤ በምዕራብ ደቡብ – ተምቤን እና አዴት ፤ በደቡብ – ገር አልታ ፤ በምስራቅ – አጋሜ ፤በሰሜን – መረብና በለሳ ናቸው:: የታሪክ ሰነዶች በአጼ ቴዎድሮስም ዘመን እንደሚነግረን ፤ ወልቃይትና ጠገዴ በትግራይ ስር አልነበሩም::

kerenite
Member
Posts: 4680
Joined: 16 Nov 2013, 13:15

Re: ታሪክ አይዋሽም!

Post by kerenite » 15 Oct 2019, 13:10

Hameddibewoyane wrote:
15 Oct 2019, 09:49
የወልቃይት፣የጠገዴ፣የካፍታ ሁመራና የጠለምት ህዝብ ጎንደሬ አማራ ኢትዮጵያዊ ነዉ።የትግራይ ኤሊቶች ወልቃይት የወልቃይት ነዉ በወልቃይት ጉዳይ የሚያገባዉ ወልቃይቴዉ ብቻ ነዉ የሚል ነጠላ ዜማ ለቀዋል።ወልቃይት ወልቃይት ነዉ፤ዋግ ዋግ ነዉ፣ራያ ራያ ነዉ፣ተምቤን ተምቤን ነዉ፣እንደርታ እንደርታ ነዉ ነገር ግን ከታሪክ አንፃር አንድ እዉነት አለ ወልቃይት ጎንደር ነዉ፤ዋግ ወሎ ነዉ፤ራያ ወሎ ነዉ፤ተምቤን ትግራይ ነዉ፤እንደርታ ትግራይ ነዉ።

መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚያዉቀዉ የወልቃይት ጠገዴ መሬት የጎንደር አካል ነዉ ስለዚህ የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም ጎንደሬ ጉዳይ ነው።ወልቃይት ጠገዴ መሬቱም ህዝቡም አማራ ነው ስለዚህ የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም አማራ ጉዳይ ነዉ። የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከመላዉ የጎንደር ህዝብ ጋር በደም የተሳሰረ ዝምድና አለዉ።የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ የሚሉት የወልቃይት ህዝብ ከጎንደር ህዝብ ጋር ያለዉን የዘር ሀረግ ትስስር ለመበጠስና ወልቃይትን እንደ ፈለጉ ለመቆጣጠር እንድያመቻቸዉ ነዉ። የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ እያሉ የሚያዜሙት የወልቃይትን ህዝብ ከጎንደር ህዝብ ለመለየት የሚያደርጉት የስነ ልቦና ፕሮፓጋንዳ ነዉ።የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ እያሉ የሚለፍፉት ወልቃይትን ከጎንደር በመነጠል የጎንደር ክፍለ ሀገርን የግዛት አንድነት ለማፈራረስ ነዉ።

ወልቃይት የጎንደር አካል ነች!
የወልቃይት ጉዳይ የመላዉ አማራ ጉዳይ ነዉ።
Dude,

To begin with, you claim to be an eritrean, hence why do you interefere on ethio affairs?

Having said that and since ethios ignored you while in their eyes, you are slolely an irgo zimb a historically illiterate dude commenting on their affairs uninvited but as an eritrean I am trying to help.

History 101....

One cannot judge history based on a specific time. Yours was covering the era of tedros the second (1855-1868 befrenj akotater) but 100 years earlier, there was mikael sihul and the history was totally different ( read what james bruce narrated)

P.S. I believe you could be a tigriyan or posing as an eritrean. Hence, let me ask you this;

Why do tigreans have to wait for a century to come to power? Any explanation?
I tell you why:

Mikael sihul, a tigriyan, he was the defacto ruler of abyssina in the the second half of the 18th century, however, he was outsmarted by the gondere amharas and was ousted. Tigray has to wait another 100 years. In the 1850s a young monk named kahsay mircha aka atse yohannes rebelled against tedros and later, he became nguse negest but he too was outsmarted by the shoa amhara and he lost fighting the mahdis and died. That was in 1889.

Tigray has to wait for another 100 years to come to power and it happened in 1991, the tigray weyannes took power but in 2018 they lost power. When is next?
Last edited by kerenite on 15 Oct 2019, 13:39, edited 1 time in total.

Hameddibewoyane
Member
Posts: 3890
Joined: 25 Sep 2019, 02:42

Re: ታሪክ አይዋሽም!

Post by Hameddibewoyane » 15 Oct 2019, 13:30

Do you have any concrete evidence that welkait belongs to your kilil Tigray? If so, you need to argue with facts. History has confirmed that Welkait is a fertile land of Gonder stolen by Tigray and this is confirmed by Dr. Aregawi Berhe. When are you people from Tigray argue based on facts rather than folktales? If you can not argue with facts, you better hide in your tiny kilil as usual.
kerenite wrote:
15 Oct 2019, 13:10
Hameddibewoyane wrote:
15 Oct 2019, 09:49
የወልቃይት፣የጠገዴ፣የካፍታ ሁመራና የጠለምት ህዝብ ጎንደሬ አማራ ኢትዮጵያዊ ነዉ።የትግራይ ኤሊቶች ወልቃይት የወልቃይት ነዉ በወልቃይት ጉዳይ የሚያገባዉ ወልቃይቴዉ ብቻ ነዉ የሚል ነጠላ ዜማ ለቀዋል።ወልቃይት ወልቃይት ነዉ፤ዋግ ዋግ ነዉ፣ራያ ራያ ነዉ፣ተምቤን ተምቤን ነዉ፣እንደርታ እንደርታ ነዉ ነገር ግን ከታሪክ አንፃር አንድ እዉነት አለ ወልቃይት ጎንደር ነዉ፤ዋግ ወሎ ነዉ፤ራያ ወሎ ነዉ፤ተምቤን ትግራይ ነዉ፤እንደርታ ትግራይ ነዉ።

መላዉ የኢትዮጵያ ህዝብ እንደሚያዉቀዉ የወልቃይት ጠገዴ መሬት የጎንደር አካል ነዉ ስለዚህ የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም ጎንደሬ ጉዳይ ነው።ወልቃይት ጠገዴ መሬቱም ህዝቡም አማራ ነው ስለዚህ የወልቃይት ጉዳይ የሁሉም አማራ ጉዳይ ነዉ። የወልቃይት ጠገዴ ህዝብ ከመላዉ የጎንደር ህዝብ ጋር በደም የተሳሰረ ዝምድና አለዉ።የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ የሚሉት የወልቃይት ህዝብ ከጎንደር ህዝብ ጋር ያለዉን የዘር ሀረግ ትስስር ለመበጠስና ወልቃይትን እንደ ፈለጉ ለመቆጣጠር እንድያመቻቸዉ ነዉ። የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ እያሉ የሚያዜሙት የወልቃይትን ህዝብ ከጎንደር ህዝብ ለመለየት የሚያደርጉት የስነ ልቦና ፕሮፓጋንዳ ነዉ።የትግራይ ኤሊቶች የወልቃይት ጉዳይ የወልቃይት ነዉ እያሉ የሚለፍፉት ወልቃይትን ከጎንደር በመነጠል የጎንደር ክፍለ ሀገርን የግዛት አንድነት ለማፈራረስ ነዉ።

ወልቃይት የጎንደር አካል ነች!
የወልቃይት ጉዳይ የመላዉ አማራ ጉዳይ ነዉ።
Dude,

To begin with, you claim to be an eritrean, hence why do you interefere on ethio affairs?

Having said that and since ethios ignored you while in their eyes, you are slolely an irgo zimb a historically illiterate dude commenting on their affairs uninvited but as an eritrean I am trying to help.

History 101....

One cannot judge history based on a specific time. Yours was covering the era of tedros the second (1855-1868 befrenj akotater) but 100 years earlier, there was mikael sihul and the history was totally different ( read what james bruce narrated)

P.S. I believe you could be a tigriyan or posing as an eritrean. Hence, let me ask you this;

Why do tigreans have to wait for a century to come to power? Any explanation?
I tell you why:

Mikael sihul, a tigriyan, he was the defacto ruler of abyssina in the the second half of the 18th century, however, he was outsmarted by the gondere amharas and was ousted. Tigray has to wait another 100 years. In the 1850s a young monk named kahsay mircha aka atse yohannes rebelled against tedros and later, he became nguse negest but he too was outsmarted by the shoa amhara and he lost fighting the mahdis and died. That was in 1889.

Tigray has to wait for another 100 years to come to power and it happened in 1991, the tigray weyannes took power but in 2018 they lost power. When is next?

Za-Ilmaknun
Member
Posts: 4486
Joined: 15 Jun 2018, 17:40

Re: ታሪክ አይዋሽም!

Post by Za-Ilmaknun » 15 Oct 2019, 15:34

There is no any credible evidence that attests to Humera and Raya being part of Tigrai at any point in the history of the Country. TPLF annexed those lands and killed the indigenous people and populated the land by its ex-fighters. It is a matter of time before historical injustices are corrected once and for all. WolQait has never been a a territory under Tigrai until 1991.

Temt
Member+
Posts: 5419
Joined: 04 Jun 2013, 22:23

Re: ታሪክ አይዋሽም!

Post by Temt » 15 Oct 2019, 15:51

Za-Ilmaknun wrote:
15 Oct 2019, 15:34
There is no any credible evidence that attests to Humera and Raya being part of Tigrai at any point in the history of the Country. TPLF annexed those lands and killed the indigenous people and populated the land by its ex-fighters. It is a matter of time before historical injustices are corrected once and for all. WolQait has never been a a territory under Tigrai until 1991.
Yes, that is true to everyone who believes in the rule of law, but not to the jihadi ጋዕጋዕ ዑጉም Eritrea- pretender, Koremite.

Post Reply