Ethiopian News, Current Affairs and Opinion Forum
-
Revelations
- Senior Member+
- Posts: 34573
- Joined: 06 Jan 2007, 15:44
Post
by Revelations » 02 Sep 2019, 07:42
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ ዛሬ ÷ነሐሴ 27 ቀን 2011 ዓ.ም አሰቸኳይ ስብሰባ ተቀመጠ፡፡ ለቋሚ ሲኖዶሱ አስቸኳይ ስብሰባ መቀመጥ ምክንያት የሆነው ደግሞ ÷ትናት ነሐሴ 26 ቀን 2011 ዓ.ም ራሱን የኦሮሚያ ‹‹ቤተ ክህነት›› አደራጅ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ሕገ ወጥ ስብስብ÷የቋሚ ሲኖዶሱን ዕግድ በመተላለፍ ዛቻዊ መግለጨ መስጠቱን ተከትሎ ነው፡፡
ቤተ ክርስቲያኒቱ ከሰላም ሚኒስተቴር ሚኒስትር ወ/ሮ ሙፈሪሃት ካሚል እና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ታከለ ኡማ ጋር በፓትርያርኩ ጽ/ቤት በተለያዩ ቀናት በጉዳዩ ላይ መነጋገራቸውና ባለሥልጣናቱም ተገቢውን የእርምት ርምጃ እንደሚወስዱ ቃል መግባታቸውን የሚገልጡት የውይይቱ ተሳታፊ የሆኑ ጳጳሳት፤ሁለቱም ባለሥልጣናት ለቃላቸው ያልታመኑ ሆነው እንዳገኟቸውና፤ እንደውም ሕገ ወጡ ስብስብ በመንግሥተ ተቋም ቢሮ ውስጥ ዛቻዊ መግለጫ ሲሰጥ ዝምታን መምረጣቸው በእነርሱና በስብስቡ መካካል ተጓደኝነት እንዳለ አማላካች ነው ሲሉም ገልጠዋል፡፡
ራሱን የኦሮሚያ ‹‹ቤተ ክህነት›› አደራጅ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራው ስብስብ ሕገ ወጥ መሆኑንና በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ስም የሚሰጠውንም መግለጫ መንግሥት እንዲያስቆም ቋሚ ሲኖዶስ ለመንግሥት ጥሪ ማድረጉን የሚያስታውሱ ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፤ በሕግ ፊት ሕጋዊ ሰውነት ያላትን ቤተ ክርስቲያን በሕገ ወጥ ስብስ እንድትጠቃ ሆን ብሎ መንግሥት ፈቅዷል ሲሉ እየተደመጡ ነው፡፡ከዚህ በኋላ ፍልሚያው ከሕገ ወጥ ስብስቡ ብቻ ጋር አይደለም የሚሉት ብፁዓን አበው፤መንግሥት ለሕገ ወጥ ስብስቡ ከለላ እየሆነ የሚቀጥል ከሆነ ፍልሚያው ከመንግሥትም ጋር እንደሚሆንም እያሳሰቡ ነው፡፡በተለይ ለጊዜው ስማቸውን እንዳልጠቅስ ያሳሰቡኝ አንድ አረጋዊ ሊቀ ጳጳስ ‹‹ሞት አንድ ጊዜ ነው፤ክብር ለዘላለም ነው፡፡እኔ እንዶነ የምሞትላት ቤተ ክርስቲያን እንጂ የምሞትለት ብሔር የለኝም፡፡እንዲኖረኝም አልፈቅድም፡፡ክርስቶስ ለሰው ሞተ እንጂ ለብሔር አልሞተም፡፡››ይሉና መንግሥት ጊዜው ሳይረፍድ ቢያስብበት ለራሱ መልካም ነው ብለዋል፡፡
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በዛሬው ስብሰባ ራሱን የኦሮሚያ ‹‹ቤተ ክህነት›› አደራጅ ኮሚቴ ብሎ የሚጠራውን ሕገ ወጥ ስብስብ የተመለከተ እና መንግሥት ላይ ጠበቅ ያለ ውሳኔ ያሳልፋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ቤተ ክርስቲያኒቱ በአዲስ አበባ መስተዳደር አስተባበሪነት ጳጎሜ 3 ቀን 2011 ዓ.ም ከሚካሔደው ‹‹ብሔራዊ የኩራት ቀን ›› ከተኘው መርሐ ግብር እና በፌደራል መንግሥት ደረጃ ከሚዘጋጁ ልዮ ልዮ መርሐ ግብሮችም ራሷን እሰከማግለል የሚያደርሱ ውሳኔዎች ልትወስን ትችላለች፡፡

-
Ethoash
- Senior Member+
- Posts: 26144
- Joined: 20 Apr 2013, 20:24
Post
by Ethoash » 02 Sep 2019, 08:48
how many of them are Tigray, oromo, Gurage, southern etc...
አሰቸኳይ ስብሰባ ተቀመጠ to fix ethnic makeup(ስብጥር) or to stop ethnic makeup
-
kibramlak
- Member
- Posts: 2155
- Joined: 26 Sep 2013, 09:27
Post
by kibramlak » 02 Sep 2019, 08:59
እንተ አህያ የሰው ሰገራ፣፣ ኢትዮጵያ እምትባል ሀገር እምትበጠበጥ እስከሆነ ድረስ የገዛ እናትህን ከMebdat እምትመለስ አደለህም
Ethoash wrote: ↑02 Sep 2019, 08:48
how many of them are Tigray, oromo, Gurage, southern etc...
አሰቸኳይ ስብሰባ ተቀመጠ to fix ethnic makeup(ስብጥር) or to stop ethnic makeup
-
Ethoash
- Senior Member+
- Posts: 26144
- Joined: 20 Apr 2013, 20:24
Post
by Ethoash » 02 Sep 2019, 09:09
kibramlak wrote: ↑02 Sep 2019, 08:59
እንተ አህያ የሰው ሰገራ፣፣ ኢትዮጵያ እምትባል ሀገር እምትበጠበጥ እስከሆነ ድረስ የገዛ እናትህን ከMebdat እምትመለስ አደለህም
this two የአማራ ቄሶች support Afan oromo service they r telling የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ doesnt mean የየአማራ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ
do u know የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ were all Egyptian until Italy come and make it all Tigray ሲኖዶስ then the Amhara took over