ኢትዮጵያ ይህን የመሰለች የደስታ ሲቃ የምታሲዝ አገር ሆናለች! እኔ መላ ሕይወቴን ያደረኩት መስዋዕትነት ተመልሶልኛል!
ሕዝቦቼ ይህ እንዲሆኑ ነበር መላ ሕይወቴን ፖለቲካ ውስጥ ያጠፋሁት! አሚን
Last edited by Horus on 22 Mar 2026, 19:17, edited 3 times in total.
Re: ኢትዮጵያ ይህን የመሰለች የደስታ ሲቃ የምታሲዝ አገር ሆናለች! እኔ መላ ሕይወቴን ያደረኩት መስዋዕትነት ተመልሶልኛል!
ኣዲሱ ኪዳኑ፣ ዛሬ ደግሞ አሙን ኣልክ?
ፕሮፌሰር ቃሎ በኖረበት ዘመን እየኖርክ?
ባለፉት ብዙ ዓመታት አረም እያልክ፣ ልንቀል እያልክ ስትለፋ ኖረሃል።
እየለፋህ ስትዋዥቅ፣ ለሃገር ጽናት ስትመከርም ኖረሃል።
የሃገር ጽናት ዋጋን እንደ አየር ጠባይ እና መርካቶ ሸቀጥ ስትቀያይርም ኖረሃል።
ዛሬ አሙን ያልክ የአሙን ደብዳቤ ሚዛናዊ መሆኑን ኣዉቀሃል?
በአሙን ከለላ ስር በሰበብ ኣስባቡ የሙሉ ህይወት ትግል ከሰሜን እስከ ደቡብ እና ከምስራቅ እስከ ምዕራብ በጥቂቱ፥
ኣፄ ቴዎድሮስ፣ ኣፄ ዮሓንስ፣ አቡነ ጴጥሮስ፣ ዘርዓይ ደረስ፣ ኣፄ ሀይለ ስላሴ፣ ጄነራል አማን ኣንዶም፣ ጄነራል ታደሰ ብሩ፣ ዶክተር ሀይሌ ፍዳ፣ ዶክተር ሰናይ ልኬ፣ ጄነራል ደምሴ ቡልቶ፣ ጄነራል ፋንታ በላይ፣ በዾ ደቻሳ፣ ባሮ ቱምሳ፣ ነዺ ገመዳ፣ ቡሪሶ ቦሩ፣ ሀየሎም አርዓያ፣ ከኤርትራ በረሃ እስከ ትግራይ ተራራ፣ ስንቶችን ታሪክ ይቁጠር።
ስ ህን አመኑ ያ ዱአ፣ ኢትዮጵያ ጣዖት ናት፣ ታቦት ጣዖት ነዉ ያለዉ ወዳጅህ እነዚህን ሁሉ ብያንስ በስም የማያዉቅ ኣይዴለም።
የሚገርመዉ የማይነጥፉ የአሙን ተዓምራት የተገለጡት በኣንተ በኩል ሳይሆን ለሃገር ጽናት ሰበበኛዉ መንግስቱ ሀይለማርያም ባሰራዉ ትምህርት ቤት በሉል መሆኑ ነዉ።
-
ethiopianunity
- Senior Member
- Posts: 10949
- Joined: 30 Apr 2007, 17:38
Re: ኢትዮጵያ ይህን የመሰለች የደስታ ሲቃ የምታሲዝ አገር ሆናለች! እኔ መላ ሕይወቴን ያደረኩት መስዋዕትነት ተመልሶልኛል!
ጦርነት በሱዳንና በአኢትዮዽያ ድንበር ተጀምሯል ይለናል አንዱ እውነት ከሆነ፣ ህዝብን ለማስተኛት ይሆን አላስፈላጊ ሽርጉድ አገርውስጥ በተለይ በአገራችን ጉረቤትና አጠገባችን አረብ አገራት ጦርነት እየተጧጧፈ እኛን የማይነካን ይመስለሀል?