(ጨቅላው) - እናንተ ጅላጅል ጅላንፎች፡ አሁን ከናንተ በላይ ሻእብያን የሚያውቅ ሰው አለ?
(ምርኮኞቹ) - አረ የለም።
(ጨቅላው) - ታዲያ ምን እየጠበቃችሁ ነው፡ ወኔው የትጠፋ ለምን አትዘምቱም?
(ምርኮኞቹ) - አንተስ ከኛ ጋ አትዘምትም?
(ጨቅላው) - እኔማ ግድቡን አስገድቤላችሁ እሱን ልጠብቅ እንጂ። እናንተ ደሞ ትናንት የፈጸማችሁትን ስህተት አርሙልን።
(ምርኮኞቹ) - እንዲህ ሲል፡ ብቻውን ታምር የሚያደርግ አይመስልም።
(ጨቅላው) - ምን አልክ አንተ ጅላንፎ?
(ምርኮኞቹ) - ግን አብይ፡ እነሱ እኮ ጨወታ አያውቁም። ሲዋጉ የኡነት ነው የሚዋጉት።
(ጨቅላው) - ታድያ እናንተ ሊጥ ልታቦኩ ነው የምትሄዱት።
(ምርኮኞቹ) - አረ ወገን አንድ በሉ። ያለ መማረክ እንዲህ አፍ ያስቀድዳል? ያልተማረከ ሁሉ ጀግና የሆነ ይመስለዋል ልበል ወገን።
(ምርኮኞቹ) - ዝም በል እንዳይሰማን።
(ምርኮኞቹ) - ይስማ። ሻእብያን ብያውቀው ኑሮን አቢቹ እንዲህ አይቀደድም ነበር። መሄዳችን ካልቀረ ግን እንደተለመደው።
(ምርኮኞቹ) - ምን?
(ምርኮኞቹ) - እውነትም ጅላንፎች!! ለሶስተኛ ግዜ ለመማረክማ አላደርገውም። እዛ ማን እንደሚጠብቀን እያወቃችሁ። አሁን እኮ እነ ወዲ ፈራዳይ የሉም።
ሰናይ ሰሎሞን (ወዲ መምህር)
